16 ሰዎች የተገደሉበት የድሮን ጥቃት በአማራ ክልል

February 24, 2025
ባለፈው ሳምንት ሃሙስ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ “አንገሽ” ቀበሌ ተፈፀመ በተባለ የድሮን ጥቃት 16 ሠዎች ሲገደሉ 10 ያክል መቁሰላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ። ጥቃቱ የተፈፀመው በሱቆችና ሻይ ቤቶች በነበሩ ንፁሐን ዜጎች ላይ እንደሆነ ነዋሪዎቹ ገልፀዋል። የአካባቢው የመንግሥት አስተዳደር ደግሞ ጥቃቱ የፋኖ ታጣቂዎች እንደመጠለያ በሚገለገሉበት ትምህርት ቤት ላይ መሆኑነና ሟቾቹም ታጣቂዎች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። ከአንድ ዓመት በላይ የሆነዉ እና እስካሁንም መሻሻል ያልታየበት የአማራ ክልል የሠላም እጦት አሁንም ለነዋሪዎቹ እንግልት፣ ጉስቁልና፣ ስቃይና ስጋት ሆኖ እንደቀጠለ ነው። ጦርነቱን ተከትሎ በርካታ የድሮን ጥቃቶች ተፈፅመዋል፣ በርካቶችም ህይወታቸው አልፏል፤ የአካል ጉዳትም የደረሰባቸው ብዙዎች ናቸው። በምሽቱ ስርጭታችን ዘገባ ይዘናል፤ ተከታተሉን!
DW Amharic
Previous Story

ኮሎኔል ፉንታሁንን ለመግደል መሞከር! የብልጽግና ፍላጎት የብአዴን ተልዕኮ!

Next Story

ይድረስ ለውድ የክፉ ዘመን ጓዴ ፕሮ. ፍቅሬ ቶሎሣ – ከወንድምህ ይነጋል በላቸው

Latest from Same Tags

የአማራና የኦሮሙማ ድርድር – በሣቅ አትግደሉን!

ይነጋል በላቸው “አማራ በድርድር የሚፈታ ችግር አልገጠመውም” በሚል ርዕስ በፈረንጆቹ አቆጣጠር Sept. 16, 2023 የሚከተለውን መጣጥፍ ጽፌ እንቅልፍ ሳይበግራቸው፣ ድካም ወፃማ ሳይፈታቸው ለሀገራቸው ትንሣኤ

እስክንድር ነጋ በታዛቢዎች አማካይነት ከአቢይ አህመድ ጋር የሚያደርገው ድርድር የአማራውን ህዝብ የተሟላ ነፃነት የሚያጎናፅፈው ወይስ ለዝንተ-ዓለም ኋላ ቀር ሆኖና ኑሮው ጨልሞበት እንዲቀር የሚያደርገው ?

ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)  ጥር 19፣ 2017(January 27, 2025) ሰሞኑን እስክንድር ነጋ “እመራዋለሁ የሚለውን የፋኖ ክንፍ” በመወከል ከአቢይ አህመድ አገዛዝ ጋር፣ እሱ እንደሚለው ውይይት፣ በመሰረቱ ድርድር እንዳደረገ በተለይም እነ

ጦርነቱ አማራ ክልል ብቻ ከመሰለን ተሳስተናል!

ይነጋል በላቸው የኦሮሙማ መንጋ ኢትዮጵያን በአጠቃላይ፣ አማራን ደግሞ በተለይ ከምድረ ገጽ ለማጥፋት የአራት ኪሎን ቤተ መንግሥት ከተቆጣጠረ ስድስተኛውን ዓመት አጠናቆ የሰባተኛው እኩሌታ ላይ ደርሷል፡፡
Go toTop

Don't Miss