የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ በየሰብአዊ እርዳታ በጫኑ ተሽከርካሪዎች ያልተፈቀደ ጥሬ ገንዘብ እና ቁሳቁሶችን የማስተላለፍ ተግባርን በጽኑ አወገዘ

July 30, 2022
በአፋር ክልል ሰርዶ ኬላ ጣቢያ በተደረገ ፍተሻ ወደ ትግራይ ክልል አስቸኳይ ድጋፍ እና የሕክምና ግብአቶችን በጫነ ተሽከርካሪ ውስጥ ገንዘብ እና ፈቃድ ያላገኙ እቃዎች ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ሊዘዋወር ሲል መያዙን ገልጿል።
ድርጊቱን የፈጸመው አሽከርካሪ በቁጥጥር ስር መዋሉንና ተሽከርካሪው ኮሚቴው ከአንድ የንግድ ኩባንያ ለአጭር ጊዜ በኪራይ የወሰደው መሆኑን አመልክቷል።
የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ “ከተገኘው ገንዘብ እና እቃዎች ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የለኝም ድርጊቱን አጥብቄ አወግዛለሁ” ብሏል በመግለጫው።
ኮሚቴው “በመላው ኢትዮጵያ በትጥቅ ግጭት እና ሌሎች ሁከቶች” የተጎዱ ሰዎችን ብቻ መርዳት የሚፈልግ የሰብአዊ ድርጅት እንደሆነና በኪራይ ያመጣው ከባድ የመኪና አሽከርካሪ ያጋጠመው ሁኔታ በስራው ላይ ተጽእኖ እንዳያሳድር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።
በአፋር ክልል ጉምሩክ ኮሚሽን የሰመራ ቅርንጫፍ ዱብቲ ወረዳ ሰርዶ መቆጣጠሪያ ጣቢያ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ8 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ እና የተለያዩ ያልተፈቀዱ ቁሳቁሶችን መያዙ ይታወቃል።
ኢዜአ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የባልደራስ ተወካይ ከአሜሪካ መንግስት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልእክተኛ ጋር ተወያየ

Next Story

አንተ ምንጭ ሆይ ፍለቅ!

Go toTop