የአማራና አፋር ተጎራባች ወንድማማቾች የሰላም መድረክ በቀወት ወረዳ ኩሬ በረት ቀበሌ በመካሄድ ላይ ነው!

January 13, 2022
የአንድ እናት ሀገራቸውን ህመም በጋራ የታመሙ፣በፍቅርና ህብረት በጋራ ተቀናጅተው ሀገር አፍራሽ አሸባሪዎችን በጋራ የቀጡት በሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ የራሳ ማህበረሰብና የአፋር ወንድሞቻቸው የጋራ ምክክር በቀወት ወረዳ ኩሬ በረት ቀበሌ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በምክክር መድረኩ ላይ የሰሜን ሸዋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ሲሳይ ወልደአማኑኤል፣ የአፋር ዞን 5 ሀረር ራሱ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ ማቴ፣ የሰሙ ሮቢ ገለአሎ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሀሰን ሀንድዬ እንዲሁም የቀወት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሾመ ሸዋዬን ጨምሮ በርካታ አመራሮችና ከሁለቱም ህዝብ የተውጣጡ በርካታ ተወካዮች ታድመዋል።
የሁለቱ ወንድማማቾች የጋራ የሰላም መድረክ ከዚህ በፊት በአፋር ክልል ዞን 5 ሰሙሮቢ ገለአሎ ወረዳ መካሄዱ ይታወሳል።
በዝርዝር ዘገባ የምንመለስበት ይሆናል።
መረጃው የሰሜን ሽዋ ዞን የዲጂታልና የማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ህወሀት ኢትዮጵያን እንዲዘረፍ መንገድ የከፈተው ህገ መንግስት! – በሰዋለ በለው

Next Story

ምንም ይሁን ምን ዲያስፖራው ቅሬታውን አይደብቅም፣

Go toTop