በአማራ ክልል በሚደረገዉ ጦርነት ምክንያት ከ6 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ለርሀብ ተጋልጠዋል

November 9, 2021
ዓለምአቀፍ ረጂ ድርጅቶች በጦርነት ቀጠና ላሉ ወገኖች እርዳታ ለማቅረብ ከክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን ያደረጉ ቢሆንም እስካሁን ግን ለሕዝቡ ርዳታ አለመስጠታቸዉን አቶ ዘላለም አስታዉቀዋል።
አስቸኳይ ርዳታ የሚሻዉ 6 ሚሊዮን ሕዝብ እርዳታ ባለማግኘቱ ሕብረተሰቡ ከተጋረጠበት አደጋ በራሱ ትግል ሊወጣ እንደሚገባ ኮሚሽነር ዘላለም መምከራቸዉን የባሕርዳሩ ወኪላችን የዓለምነው መኮንን ዘገቧል።
ይህን የዘገበው DW ከሁለት ቀናት በፊት ። ሌሎችም ሚዲያዎች ዘግበውታል።
የምጽፈው ይነበቧችኋል ? 6 ሚሊየን ለረሃብ ተጋልጧል ነው’ኮ የሚሉት ።
ታዲያ ይሄን እያዩ እየሰሙ ዝም ይባላል ወይ ?
መላ አይፈለግም ወይ ?
አይቶ እንዳላየስ ይታለፋል ወይ ?
ሰበር ዜና ተያዘ ተለቀቀ እየተባለ ህዝብ እያለቀ ዝም ይባላል ወይ ?
ዜናው ከ 4 ቀን በፊት የወጣ ነው። ሰበር ዜና ያልኳችሁ ሰበር ዜና ካልተባልን የወገኖቻችን ያሉበትን መረዳት ስላቃተን ነው ።
Via abdurahim ahmed

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

አፍሪካ ህብረት ልዩ ልዑክ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፤ ዛሬ የአማራ እና የአፋር ክልሎችን ይጎበኛሉ

Next Story

ለራሷ ያላወቀች ለቅዱስ ገብርኤል መድኃኒት ጠየቀች !

Go toTop