የሕወሃት ኃይሎች ስልታዊቷን የደሴ ከተማን መቆጣጠራቸውን ትናንት ቅዳሜ ካስታወቁ በኋላ የመንግስት ኃይሎች በከተማዋ ዛሬ እሁድ አዲስ ውግያ መክፈታቸው ተሰማ

October 31, 2021
የጥቅምት 21 ቀን 2014 ዓ/ም የዓለም ዜና በድምጽ
ርዕሶቹ
• የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መቀሌ ከተማ አቅራቢያ በሚገኝ የህወሃት ኃይሎች ማሰልጠኛ ጣብያ ላይ ያነጣጠረ የአየር ጥቃት ማድረሱን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስቴር ዐስታወቀ።
• በሱዳን የዴሞክራሲ ተሟጋች ቡድኖች ትናንት ጠርተውት በነበረው የህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ ላይ ፖሊስ በከፈተው ተኩስ በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች ሳይገደሉ እንዳልቀሩ የህክምና ምንጮች ገለጹ። ፖሊስ በከፈተው ተኩስ ከሞቱት በተጨማሪ ከ100 በላይ ሰዎች ቆስለው ወደ ሕክምና ተወስደዋል።
• በምጣኔ ሃብት የበለጸጉት የቡድን 20 አባል ሀገራት መሪዎች በውጭ ሀገራት በድንጋይ ከሰል ኃይል ለማመንጨት የሚያደርጉት የገንዘብ ድጋፍ እንዲያበቃ ከስምምነት ደረሱ። አባል ሃገራቱ ጣልያን ሮም ውስጥ ለሁለት ቀናት ሲያካሄዱ የነበረውን ስብሰባቸውን ዛሬ ሲያጠናቅቁ ባወጡት መግለጫ በጎርጎርሳውያኑ የክፍለ ዘመኑ እኩሌታ አልያም በተቀራረበ ጊዜ የካርቦን ልቀትን በምድር ላይ የተጣጣመ እንዲሆን የተያዘውን መርኃ ግብር ለማሳካት እንደሚጥሩ አስታውቀዋል።
DW

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የአገር መከላከያ ሠራዊት በሁሉም ግንባሮች አሸባሪውን ወራሪ የህወሃት ሃይል በመደምሰስ ላይ እንደሚገኝ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ

Next Story

አይዞን ወሎ (አሁንገና ዓለማየሁ)

Go toTop