የመግለጫ ጋጋታ ከጥቃት አያድንም፤ #ነፃነት በነፃ የለም፤ ከንግሥት ይርጋ (ጎንደር)

October 31, 2021
ንግሥት ይርጋ (ጎንደር)
ከክልል እስከ ወረዳ ያለ አመራር በአግባቡ ኃላፊነቱን እየተወጣ አይደለም :: ይህን ስል በእጣት የሚቆጠሩ ምሳሌ የሚሆኑትን አመራሮች አይጨምርም ::
በየግንባሩ “እያዋጋን ነው” የሚሉ አመራሮችን አሉበት በተባለው በቦታው እየተንቀሳቀስኩ አይቻለሁ :: በሕዝብ በጀት ሆቴል ተቀምጦ የምግብ እና የመጠጥ በጀት ከመፍጀት ውጪ ግንባር ገብቶ የድርሻውን ወይም ግዴታውን የሚወጣ አመራር የለንም :: አስተያየት ስንሰጥም በጥርስ ውስጥ እንገባለን ::
የሚሠሩ አመራሮችን ምሳሌ አድርገን ስንናገር ጓ-ገጭ የሚለው ብዙ ነው ::
አሻጥር አለ ለሚባለው አሉባልታ እንደ እኔ በመከላከያ ሠራዊታችን ላይ ምንም ዓይነት አሻጥር አለ ብየ አላምንም :: ወታደሩ የሚችለውን ያክል ዋጋ እየከፈለ እየተዋደቀ በዓይኔ እያየሁ ነው ::
ግን ትእዛዙ ከየት እና ለምን እንደሆነ ባናውቅም ፤ በውጊያ ስዓት ላይ “ውጊያውን አቁሙ” የሚል ትዛዝ ይሰጣል :: ወታደር ለምን ? እንዴት ? የሚባል ጥያቄ ማንሳት አይቻልም ምክንያቱም ትእዛዙን የሚሰጡት ፖለቲከኞች ናቸው ::
እንደ እኔ እይታ ሕዝባችን መሪ አልባ ነው:: መንግሥት ምን አለ ? ከማለት እና የመንግሥትን ዲስኩር እና #የመግለጫ ጋጋታ ከመጠበቅ ወጥተን ሁላችንም የምንችል ገብተን በመዋጋት ወይም ስንቅ በማቀበል አለዚያም ቁስለኛ በማንሳት እና በማገዝ ለመከላከያ ሠራዊታችን ለዐማራ ልዩ ኃይል ለፋኖ እና ለምንሻችን የኋላ ደጀን በመሆን ለነፃነታችን እንታገል::
በክልል እና በወረዳ አመራሮች ተስፋ የምታደርግ እርምህን አውጣ :: የእኛ አመራሮች መግዚትነቱን ለምደውታል :: በዚህ ስዓት የህልውና ትግል ከፊታችን ተደቅኖ ሰዎች ስለሥልጣን እከሌ ተሾመ እከሌ ተንሳፈፈ ሲሉ ነው የሚውሉ :: ለሄደ ለመጣው ማሸርገድ ልምዳቸው ነው::
እስካሁን ዋጋ እየከፈለም እየሞተም ያለ መከላከያ ወይም ልዩ ኃይል ፋኖ ምንሻ እንጅ አመራር ከተንደላቀቀ ሆቴል ወጥቶ እንደ ሕውሀት በችግር ጫካ ገብቶ የታገለና ያታገለ የለም ::
ወንድ ሆነው ማታገሉን አያታግሉ ግን የሆነ ከተማ ስጋት ላይ ሲሆን ቀድመው በመፈርጠጥ ሕዝቡን ውዥንብር ውሰጥ ከተው የሚጠፉትን ብታዩ ያሳፍራል:: ነገሩ ሲያልፍ ጠብቀው ተመልሰው አክተር (የድሉ ባለቤት ) ይሆናሉ :: ስለዚህ #ነፃነት በነፃ የለም የመጣውን ጠላት እንደ ሕዝብ መታገል ያስፈልጋል ::
በእየቤታችን ተቀምጠን የግዞትን ቀን አንጠብቅ መብትና ግዴታችን ካወቅን ከሊቅ እስከ ደቂቅ ወጥተን ግዴታችን እንወጣ ሌላው ሙቶ እኔ ልኑር እሳቤአችን እናስወግድ ::
ድል ዋጋ እየከፈሉ ላሉ ጀግኖቻችን!!!

ጊዜ ለኩሉ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ደሴን ለመውረር አሰፍስፎ የነበረ አሸባሪው የሕወሓት ወራሪ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል

Next Story

በኢትዮጵያዊያን እየተመከተ ያለው የአሸባሪው ሕወሓት ወረራ

Go toTop