ህዳሴ ግድብን ለማደናቀፍ ማሰብ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ጉዳይ እንደማይደራደሩ ካለመረዳት የሚመነጭ ነው – ሌ/ጄ አስራት ዴኔሮ

September 22, 2021

የምድር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል አስራት ዴኔሮ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች ታላቁ የህዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ፣ ለፕሮጀክቱ መሳካት እየተከናወነ ያለውን እረፍት አልባ የሰራዊቱ የግዳጅ አፈፃፀም አድንቀዋል፤ ምስጋናም አቅርበዋል።
ጄነራል መኮንኑ በጉብኝቱ ወቅት የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን ለማደናቀፍ ማሰብ ኢትዮጵያውያን በሃገራቸው ጉዳይ እንደማይደራደሩ በቅጡ ካለመረዳት የሚመነጭ ነው ብለዋል።
አክለውም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማስተጓጎል ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚንቀሳቀሱ የውክልና ጦር አስፈፃሚ ቅጥረኛ ኃይሎች መቼም አይሳካላቸውም ማለታቸውን ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የፌስቡክ ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC

Leave a Reply

Your email address will not be published.

merera 2
Previous Story

ኦፌኮ በአመራር አባላቱ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ህልውናው አደጋ ላይ ወድቋል

mekonen 2
Next Story

ኒቼና የኦሾ ፍልስፍና እንደገና መጠናት ያለበት ነው ፡፡ የቀደመ ሃሰብ ያዘ ነውና ! – መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

Go toTop