መስሎህ ነበር (ዘ-ጌርሣም)

July 29, 2020

የረጅም ጊዜ ተንኮላቸው ሳይገባህ
አጀንዳቸውን ሳታነብና ሳይረዳህ

በቋንቋና በባህል አሳበው
መገንጠል አለብህ ብለው አታለው
አንድ ርምጃ ወደፊት አራት ርምጃ ወደኋላ ስበው

የልጆችህን ዕድል አጨልመው
ያንተንም ህይወት አደንቁረው
ከአቅምህ በላይ ክቡር ብለው
ከህዝብ ጋር አጣልተው
የጥላቻ መርዝን ረጭተው

ባልና ሚስትን አለያይተው
ቤተሰባቸውን በትነው
አንተንም አስረውና ገርፈው
ሰብዕናህን አዋርደው
እንደከብት በሜዳ ላይ ነድተው

በእግረ ሙቅ ሲጠብሱህ
በጥይት ሲደበድቡህ
ዘቅዝቀው ሲያሰቃዩህ
ምን ፀፀትና እሮሮ ተሰማህ ??

አንተማ መስሎህ ነበር
ኢትዮጵያ የምትበተንና የምትገነጣጠል

ዓላማህ አንተኑ የሚያጠፋ ሳይመስልህ
አገር መበታተን እንዲህ ቀላል መስሎህ
ታሪክን በደንብ ባለማንበብህ
ወንድሜ ለዚህ ሁሉ ስቃይ በቃህ

ብልሁን የኢትዮጵያን ህዝብ መበተን
እንደማይቻል ጠላት መረዳቱን
ማውቅና ማጤን ይገባል
አልፋና ኦሜጋ ሆኖ ታትሟል

እንኳንስ የዘር ፖለቲካ አራጋቢው
የውጭ ጠላትም አፍሯል በሙከራው
ኢትዮጵያን መበተን ከንቱ ምኞት ነው

ኢትዮጵያ ማለት ጠይም ህዝብ ነው
የሀበሻነት መለያ ያለው
ከመንፈሳዊ ህግጋት ጋር አብሮ የኖረ
መንግሥት ሳይኖር እራሱን ያስተዳደረ

ተዋልዶና ተካብዶ የሚኖር
ለጠላት ሴራ የማይበገር
ብልህና አስተዋይ ህዝብ ነው
ሊከበርና ሊደነቅ የሚገባው

አንተማ መስሎህ ነበር
ህዝብን በማጣላትና በማናቆር
ደልቶህና ተደስተህ የምትኖር

ስልጣን ከደጅህ ድረስ ሲመጣልህ
ለይስሙላ ፕረዝደንት ተብለህ
በልዩ ልዩ ማዕረጎች ሲክቡህ

ጀኔራል ኮሎኔል ሻለቃ ሲሉህ
መትረየስና ክላሽንኮ ያለጥይት ተሽክመህ
መልሶ አንተኑ የሚያስመታህ

ከወገንህ አጣልተው
የጥላቻ መርዝ ግተው
በዘርና ጎጥ ሁከት አስነስተው

እንደ ጭቃ አቡክተው
አንደ ብረት አቅልጠው
መልሰው ሲያጠቁህ ተረዳኸው ??

ሲያዘጋጁህ ለዕኩይ ተግባር
ማጣፊያ ለሌለው መደናበር
አንተማ መስሎህ ነበር
ኢትዮጵያን መበተን ቀላል ነገር

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ለሁሉም ጊዜ አለው! የዓባይ ትንቢቱ ሲፈጸም – በገ/ክርስቶስ ዓባይ

Next Story

ኦሪት ዘፍጥረት ኦሮሞ ከውሃ ነው የመጣው! የእርግማን ትውልድ! – ሰርፀ ደስታ

Go toTop