እሳት አቃጠለኝ! – በላይነህ አባተ

February 16, 2020

ጠላቴ ሌት ተቀን ሴራ ሲያሴርብኝ፣
በጨለማው ዘመን ብርሃን ከጅሎኝ፣
አጠንክሬ አካሌን ጨምቄ አይምሮዬን፣
በአስታቡልቡል ዘዴ እሳትን ፈጠርኩኝ፡፡

የፈጠርኩት እሳት እኔን እያሞቀኝ፣
ጨለማን ገሽልጦ ሌባውን ሲያሳየኝ፣
ድል ስላበሰለ ለዓመታት ደስ አለኝ፡፡

የድሉን እንጀራ ተምጣድ ሳልስበው፣
እባብ አፍ አውጥቶ ኢሳት ሲሳይ ሲለው፣
እንደ ሄዋን ስቶ ወዲያው አሳረረው፡፡

እንጨት ለቃቅሜ የቀለብኩት እሳት፣
ዕጸ-በለስ ጎርሶ እባብ የጠራው ለት፣
እሳቱ ሲሳይ ነው ይማሰል ያለ ወቅት፣
በነበልባል ምላስ ገረፈኝ በክህደት፡፡

ድሮም እኔ አማረ እጄ አመድ አፋሽ ነው፣
የፈጠርኩት እሳት እያቃጠለኝ ነው!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)
የካቲት ሁለት ሺ አስራ ሁለት ዓ.ም.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ስለ ዓባይ ውሐ ግብጽና ኢትዮጵያ ማወቅ ያለባቸው – ፕሮፌሰር  ጌታቸው ኃይሌ

Next Story

አነጋጋሪው ሰባተኛው ንጉሣችን አቢይ አህመድ ዘብሔረ ኦሮሚያ – ግርማ በላይ

Go toTop