የአንበጣ መንጋ በሶማሌ፣ በኦሮሚያና በድሬደዋ ባሉ 13 ወረዳዎች ስጋት ሆኗል

April 16, 2014

(ዘ-ሐበሻ) የአንበጣ መንጋ በሶማሊያ፣ በኦሮሚያና በድሬደዋ ባሉ 13 ወረዳዎች ስጋት ሆኗል ሲል የኢትዮጵያ የግብርና ሚኒስቴር በመንግስታዊ ሚዲያዎች በኩል አስታወቀ። እንደ መግለጫው ከሆነ የአንበጣው መንጋ በቅድሚያ የታየው በሶማሊያ ክልል ቶጎ ጫሌ አካባቢ ቢሆንም ወደ ሌሎች ክልሎችም እየተዛመተ መጥቷል።

የአንበጣ መንጋው ከሶማሊላንድ ወደ ኢትዮጵያ የገባ ሲሆን በሶማሌ፣ በኦሮሚያና በድሬደዋ አስተዳደር ባሉ ወረዳዎች 14 የሚሆኑ የአንበሳ መንጋዎች መግባታቸውን አረጋግጫለሁ ሲል የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤትቱ “የአንበጣ መንጋውን 95 በመቶ መከላከል ችያለሁ፤ በሰብል ላይ ምንም አይነት ጉዳት እንዳልደረሰም” ቢልም የአካባቢው ነዋሪዎች ግን መንግስት አፋጣኝ እርምጃ አልወሰደም በሚል ይወቅሳሉ። የአንበጣ መንጋው ወደ ሌሎች ከተሞች እንዳይዛመትም ከፍተኛ ስጋት አለ ተብሏል።

Previous Story

ጓዶች በአፅቢ ከተማ አራት የዓረና አመራር አባላት ከያዙት አልጋ እንዲለቁ ተጠይቀው ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ታስረው አደሩ

Next Story

ሚሊዮኖች ድምጽ – የእሪታ ቀን ሰልፍ በሚያዚያ 26 ቀን እንደሚደረግ የአዲስ አበባ አስተዳደሩ እውቅና ሰጠ !

Go toTop