የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ለአቶ ሠማ ጥሩነህ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ተሠማ

September 21, 2022
የፍትሕ ቢሮው ለአቶ ሠማ ጥሩነህ ማስጠንቀቂያውን የሠጠው የኢትዮ 360 ሚዲያ ቅዳሜ መስከረም 8/2015 የአቶ ሠማን የትምህርት ማስረጃ ማጭበርበር አስመልክቶ በሠጠው ጥቆማ መነሻነት ተመስርቶ መሆኑ ተሰምቷል።
የፍትህ ቢሮው የሙስና ወንጀሉን ማጣራት ከመጀመሩ በፊት አቶ ሰማ ተምሮበታል ከተባለው የቻይና ዩንቨርስቲ ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ኤንድ ኢኮኖሚክስ ተምሮ የተሠጠው የ(PHD) የምስክር ወረቀት ካለ በኢትዮጵያ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የአቻ ግምቱን በማሠራት እስከ መስከረም 12/01/2015 ዓ/ም ማስረጃውን ለሶስት ተቋማት እንዲያስገባ አዝዟል።
በዚህም አንደኛ ለክልሉ ፍትሕ ቢሮው፣ ሁለተኛ ለክልሉ ሲቪል ሠርቪስ ኮሚሽን፣ ሦስተኛ ለክልሉ የብልፅግና ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ማረጃውን የማያቀርብ ከሆነ ምርመራ ማጣራት እንደሚጀምር ማስታወቁ ተሠምቷል።
ይህንን የሠሙ የትምህርት ማስረጃ ያጭበረበሩ ሌሎች ባለ ስልጣናት ጭምር ጭንቅ ውስጥ መግባታቸው ታውቋል።

ለገ ግዮን

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

በኢትዮጵያ ተፋላሚ ኃይሎች መካከል ይደረጋል ተብሎ ስለሚጠበቀው ድርድር የአሜሪካ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር ምን አሉ

የአቢይ አህመድ ጨለማ ጉዞ!
Next Story

ዕዉር ከመሪዉ ይጣላል  ፤ ለማኝ አኩፋዳዉን ይጣላል  

Go toTop