ለጀነራል ተፈራ ማሞ ተጨማሪ የ10 ቀናት ቀጠሮ ተሰጠ

May 30, 2022
የቀድሞው የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ባህርዳር አማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ የ10 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጣቸዉ፡፡ መርማሪ ፖሊስ ዛሬ ለፍርድ ቤቱ ጀነራል ተፈራ ማሞ ላይ የቀሩኝ የማሰባስባቸው ማስረጃዎች አሉኝ ሲል የ14 ቀናት ቀን ጠይቆ ነበር። የጀነራሉ ጠበቃ በበኩላቸው ቀሩ የተባሉ ማስረጃዎች ተጠርጣሪው በዋስ ቢወጣ ሊያጠፋቸውና ሊያገኛቸው የሚችሉ ባለመሆናቸው ደንበኛቸው ከፖሊስ ጣቢያ በዋስ ተለቅቀው እንዲከራከሩ ጠይቀዋል፡፡ ጠበቃ ሸጋው አለበልን ከችሎት በኋላ የዶይቼ ቬሌ ዓለምነዉ መኮንን አነጋግሯቸው ነበር፡፡
የሁለቱንም አካላት ክርክር ያዳመጠው የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተጨማሪ የ10 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል፡፡ ዛሬም ተጠርጣሪው ፍርድ ቤት በመጡበት ወቅት ቁጥሩ በዛ ያለ የፀጥታ ኃይል ከፍተኛ ጥበቃ ሲደርግ ነበር፡፡ ብርጋዴር ተፈራ ማሞ ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን የሚፃረር መልዕክቶችን በተለያዩ ሚዲያዎች ሲያስተላልፉ ነበር በሚል ተጠርጥረው በመንግስት ቁጥጥር ስር የዋሉት ግንቦት 8 ቀን 2014 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ነበር፡፡
ዘገባ ፤ዓለምነዉ መኮንን DW ከባህር ዳር/ DW

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የአማራ ሕዝብና የአጭቤ ዜናው አባት አማራጠሉ ቢቢሲ

Next Story

ባለሀብቶችን በማገት እና በማስፈራራት ብር በጠየቁ የሰራዊቱ አባላት ላይ ክስ ተመሠረተ

Go toTop