ሰበር ዜና: ኢትዪጲያዊ ሙስሊም የችሎት ውሎ (ቢቢኤን ልዩ ፕሮግራም)

December 12, 2013

ቢቢኤን ሰበር ዜና
ልዩ ፕሮግራም
ሁሉም ኢትዪጲያዊ ሙስሊም ሊሰማው የሚገባው የችሎት ውሎ
የኮሚቴዎቻችንን ጠበቆች ተማም አባቡልጉንና ጠበቃ  አዲስን አነጋገራናል፡፡ትግሉ በተጠናከረ መልኩ ለመቀጠል ህዝቡ የአሚሩን ትዛዝ በመጠበቅ ላይ ነው

[jwplayer mediaid=”10799″]

መንግስት ከሰረየሰላም አምባሳደር በሆኑት የብርቅ ሰብእና ባሌበቶች ላይ መንግስት ፖለቲካዊ ፍረጃዉን ጭኖባቸዋል፤ ይህ ደግሞ መንግስት መክሰሩን ፍንትዉ አርጎ የሚያሳይ ነዉ።በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ዉድ ዜጎች የተወከሉትን ኢትዮጵያዉያንን ፍትህ-አልባ በሆነዉ ፍርድ-ቤት ለማሸማቀቅ መሞከሩ፤ አለም-አቀፋዊ የሆኑ የህግ መስመሮችን አልፎ ሰርዓት-አልበኝነትን ለማንገስ የሚደረግ አይን-አዉጣነት በመሆኑ በዛሬዉ ችሎት መንግስት ከስሯልና እናንተ የተስፋ ባለቤት የሆናችሁ ኢትዮጵያዉያን ድል አይቀርምና ተጽናኑ።መንግስት የኛዎቹን ማንዴላዎች መፍታት ሲገባዉ ወደ እስር ቤት ልኳቸዋል። የትላንቶቹ አፓርታይዶች ኩምሽሽ-ሽምቅቅ-ስዉር እንዳሉት የዛሬዎቹም የኢትዮጵያ አፓርታይዶች ኩምሽሽ-ሽምቅቅ-ስዉር ማለታቸዉ አይቀሬ ነዉ። ልክ እንደማንዴላ ሁሉ ኮሚቴዎቻችን ከተጎናጸፉት የሰብዓዊነት ማእረግ በላይ እፁብ-ድንቅ ምድራዊ ብሎም ሰማያዊ የሆነን የብርቅ ሰብእናን እርከንን ይሻገሩ ዘንድ የፍትህ ቀበኞች ወደ እስር ቤት መልሰዋቸዋል። ድል አይቀርምና ወደ ድል በሚያሽግረዉ ሰላማዊ ታንኳ “ድምጻችን ይሰማ!” እያልን በቃልኪዳናዊ ጥምረት እንጓዝ። ልብ ያለዉ ልብ ይበል!
BBN Your Voice
Previous Story

አንድነት ፓርቲ የደቡብ አፍሪካ ኢምባሲ ተወካዩች በነገው መርሐ ግብር እንደሚገኙለት አስታወቀ

Next Story

Sport: ቀነኒሳ በቀለ በኤደንበርግ አገር አቋራጭ ውድድር ላይ እንደሚሮጥ ታወቀ

Go toTop