በረቀቀ መንገድ ተደብቆ ወደ አዲስ አበባ የገባ 4 መትረዬስ ጠብመንጃ እና ከ46 ሺ በላይ ጥይት መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሸን አስታወቀ

February 20, 2019

የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ባደረገው ክትትል በተሽከርካሪ አካል ውስጥ በረቀቀ መንገድ ተደብቆ ወደ አዲስ አበባ የገባ 4 መትረዬስ ጠብመንጃ እና ከ46 ሺ በላይ ጥይት መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሸን አስታወቀ፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=SvwytfrDZTg&t=73s

የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 አ/አ A 77608 በሆነ «አቶዝ» የቤት መኪና በባለሙያ በመፍታት ወደ አዲስ አበባ የገባ 4 መትረየስ ጠብመንጃዎች ጥር 28 ቀን 2011 ዓ/ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 አዲሱ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ ተይዞ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

በተመሳሳይ ዜና ከአማራ ብሄራዊ ክልል አዊ ዞን እንጅባራ ወረዳ በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- 53119 አ/አ የሆነ አይሱዙ ተሽከርካሪ ከከሰል ጋር በመጫን 46, 404 ልዩ ልዩ የሽጉጥ ጥይቶች ወደ አዲስ አበባ ከገባ በኋላ ጥር 30 ቀን 2011 ዓ/ም ከለሊቱ 9፡20 በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው አጂፕ ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ ከሦስት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡

Previous Story

የህዳሴው ግድብ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ለቻይናዊያን ተሰጠ

Next Story

የአባገዳዎችን ጥሪ በመቀበል የኦነግ ታጣቂዎች ወደ ካምፕ እየገባ ነው

Go toTop