አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደቱ..

January 19, 2019

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደቱ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ መቋረጡንና ላለፉት ዘጠኝ ቀናትም በግልጽ ባልታወቀ ምክንያት ተማሪዎች ወደክፍል አለመግባታቸውን ዩኒቨርሲቲው ገለጸ፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=I4V8VygwOuk&t=204s

የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት በሁለት ቀናት ውስጥ በሚደርሰው ውሳኔ መሰረትም ችግሩን ለይቶ ተገቢውን እርምጃ ለመውሰድና ተማሪዎችም ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ የሚደረግበት ሂደት እንደሚፈጠርም አስታውቋል፡፡

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ትምህርት የተቋረጠው በቅርቡ በዩኒቨርሲቲው ሦስት ልጆች ባልታወቀ ሁኔታ ሕይወታቸው አልፎ በመገኘቱ ምክንያት እንደሆነ ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም ዘግቦ ነበር::

Previous Story

የአንጋፋው የኦሮሞ አርቲስቶች ባንድ አርፈን ቀሎ አባላት ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

Next Story

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርሰቲያን ምዕመናን ዘንድ በድምቀት ተከበረ

Go toTop