የክፍለ ከተማው ባለስልጣን ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የህዝብ ገንዘብ ይዘው ተሰወሩ

January 13, 2019

በየካ ክፍለ ከተማ የወረዳ 11 አስተዳደር የኮንስትራክሽንና ህብረተሰብ ተሳትፎ ፅ/ቤት ሓላፊ የነበሩት አቶ አለም ገ/ሚካኤል ገንዘብ ይዘው ተሰወሩ፡፡ የካ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት እንዳስታወቀው ግለሰቡ ከህብረተሰቡ ለልማት ስራ የተሰበሰበ 2 ሚሊየን 70 ሺ ብር ከባንክ አውጥተው ተሰውረዋል፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=bmsf7vBqDX8
የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ፅህፈት ቤቱ አስታውቆ ህብረተሰቡም አስፈላጊውን መረጃ እንዲስጥ ጠይቋል፡፡ የምርመራ ዉጤቱን እየተከታተለ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር እንደገለፀ ከየካ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡ በቅርቡ የአዲስ አበባ አስተዳደር ከለውጡ ጋር የማይሄዱ ያላቸውን በርካታ አመራሮች በማንሳት አዳዲስ አመራሮችን እየተካ መሆኑ ይታወቃል፡፡

Previous Story

ከሜቴክ የተነጠቁት የህዳሴ ግድብ ስራዎች ለቻይና ኩባንያዎች ተሰጡ

Next Story

የኦነግ ጦር የደቡብ ዞን አዛዥ የሰላም ጥሪውን ተቀበለ

Go toTop