ደምስ በለጠ ከአገሩ ከወጣ ከ30 አመታት በኋላ ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ በገባ በ21 ቀኑ በተኛበት አርፎ ተገኘ

December 22, 2018

የአማራ ድምፅ ራዲዮ ዋና አዘጋጅ ደምስ በለጠ ከአገሩ ከወጣ ከ30 አመታት በኋላ ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ በገባ በ21 ቀኑ በተኛበት አርፎ ተገኘ::

የጋዜጠኝነት ስራውን ገና ተማሪ እያለ በሞስኮ ራዲዮ የአማርኛ ዝግጂት ክፍል የጀመረው ፤ ደምስ በለጠ ከ2016 አም ጀምሮ የአማራ ድምፅ ራዲዮ ሲያዘጋጅ ነበር። ደምስ ከረጅም ጊዜ የውጪ አገር ቆይታ በኋላ በፈረንጆቹ አቆጣጠር እሁድ ዲሴምበር 2 ቀን ኢትዮጵያ ገብቶ ነበር።

ከዛሬ 30 አመት በፊት ፤ ለትምህርት ወደ ሩሲያ ተልኮ ፤ ትምህርት ላይ እያለ በኢትዮጵያ የመንግስት ለወጥ በመደረጉ ፤ ይማርበት ከነበረበት አገር ከሩሲያ ወደ አሜሪካም ተሰድዶ ፤ ከትምህርት ዘመን በኋላ ያለውን ጊዜውን በሰሜን አሜሪካ አሳልፏል።

ደምስ በለጠ በአሜሪካ ስደት ላይ በቆየባቸው ጊዚያት ፤ በተለያዩ የራዲዮ ጣቢያዎች በጋዜጠኝነት ሰርቷል ። በተለይ በታሪካዊው የምርጫ 97 የቅንጅት ጊዜ የመጀመሪያውን “ንጋት” የተባለውን የኢንተርኔት ራዲዮ በመጀመር ፤ በአለም ላይ የተበተነውን ኢትዮጵያዊ በተመሳሳይ ሰአት ላይቭ በቀጥታ ዝግጂቱ ሲያገናኝ እንደነበር እናስታውሳለን::

ደምስ በለጠ በዚህ ብቻ ሳይገታ ፤ ከ2005 አም ጀምሮ እስከ 2012 የአውሮፓውያን ዘመን ድረስ ፤ ወደ ኤርትራ በመመላለስ ፤ በጊዜው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ይባል የነበረው ድርጅት ያደርግ የነበረውን ትግል ሲደግፍ ነበር::

ደምስ በለጠ በተለይ ተቺና አስተማሪ የሆኑ መጣጥፎቹን በተለያዩ ድረገፆች እያወጣ ያስነበበን ሲሆን ፤ በዘሃበሻ የሚወጡ ፅሁፎችንም በተገቢው መንገድ በንባብ በማቅረብ ሕዝብ የማወቅ መብት አለው የሚለውን መርህ በተግባር ያሳየ ጋዜጠኛ ነበር::
https://www.youtube.com/watch?v=FKORGOIm5_E&feature=youtu.be

Previous Story

ኤርትራዊው ፕሮፌሰር አስመሮም ለገሰ ከኢትዮጵያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ዛሬ ተነጋገሩ፡

Next Story

አቶ ለማ መገርሳ ‹‹ዶክተር አብይን በጉልበት እሳት አቀጣጥለን እናስወጣዋለን የሚሉ ከመጡ እንሟሟታታለን እንጂ አይለቅም›› አሉ

Go toTop