በነቀምት ሆስፒታል 10 እናቶች በወሊድ ምክንያት ህይወታቸው አለፈ

October 23, 2013

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በነቀምት ሆስፒታል በቅርቡ 10 እናቶች በወሊድ ምክንያት መሞታቸውን እና ፤ አንድ ሊትር ደም እስከ ሶስት ሺህ ብር መሸጡም ተጠቁሟል፡፡ በሆስፒታሉ ችግሩ እየከፋ በመሄዱ ወላድ እናቶች እና ታካሚዎች ተገቢውን የህክምና አገልግሎት ባለማግኘታቸው በዚሁ ሆስፒታል 10 እናቶች ህይወታቸው ማለፉ ተጠቁሟል፡፡

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስትም ጉዳዩን አውቆት በስብሰባ መድረክ ያነሳው ቢሆንም እስካሁን የተወሰደ እርምጃ ባለመኖሩ የሆስፒታሉ ተገልጋዮች ቅሬታ እንዳደረባቸው ኢቲዮ ምህዳር ጋዜጣ በዛሬው ዘገባ አስታውቋል፡፡ የፌደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አንድም እናት በወሊድ ምክንያት አትሞትም እያለ መፈክር ቢያስነግርም በተግባር ግን የነፍሰጡር እናቶች ህልፈት እየተባባሰ እንደሚገኝ መረጃዎች ጠቁማሉ፡፡

Previous Story

በምእራብ ሸዋ ዞን ዳኖ ወረዳ አጅላ ዳሌ እና አዋዲ ጉልፉ የሚኖሩ አማራዎች በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንገኛለን አሉ

Next Story

የጌታነህ ትሬዲንግ ባለቤት ራሳቸውን በሽጉጥ ገድለው እንዲሞቱ የተደረገበት ምስጢር ከ4 ዓመት በኋላ ወጣ

Go toTop