የጣሊያን ፖሊስ ስደተኞችን ሲቀጠቅጥ የሚያሳይ ቪድዮ (ኢትዮጵያውያንም አሉበት)

October 6, 2013

የሚከተለውን አሳዛኝ ቪድዮ ይመልከቱ” ኢትዮጵያን ለወረራ መጥቶ በጀግኖች አባቶቻችን ተዋርዶ የሄደው የጣሊያን ሰራዊት ልጅ ልጆች ዛሬ ደግሞ ስደተኛ ዜጎችን ሲቀጠቅጡ የሚያሳይ ቪድዮ በቴሌግራፍ በኩል ወጥቷል። በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የበርካታ ሀገራት ዜጎች ሱዳንን አልፈው፤ የሰሃራ በረሃን አቋርጠው ወደ ሊቢያ ከገቡ በኋላ በመርከብ ተጭነው በረጅም ስቃይ ታጅበው ጣሊያን ይገባሉ። ጣሊያን ሲገቡ ደግሞ እንዲህ ያለው አሳፋሪ ድብደባ ይደርስባቸዋል። ይህ ቪድዮ በቴሊግራፍ መጽሄት  ከተለቀቀ ቆየት ያለ ቢሆንም ሰሞኑን በጣሊያን በስደተኞች ላይ የደረሰውን አደጋና፣ አድኑን እያሉ ሌሎች ጀልባዎች እየተቃጠለች ያለችውን ጀርባ ጥለዋቸው በመሄዳቸው ለበርካታ ዜጎች ሞት ምክንያት የሆነውን አደጋ በማስታወስ በ2011 ዓ.ም የሆነውን ቪድዮውን ይመልከቱና ይፍረዱ። በነገራችን ላይ የዘ-ሐበሻ ጋዜጣና ድረ ገጽ ዋና አዘጋጅ በሰሃራ በረሃና በሊቢያ በስደት ያሳለፈ በመሆኑ ወደፊት ስለመንገዶቹና ኢትዮጵያውያኑ ስለሚገጥማቸው ፈተናዎች የሚያጫውተን ነገር ይኖራል።

Previous Story

ግንቦት ሰባት፤ ብርሀኑ፤ አንዳርጋቸው፤ የኤርትራ ነገር? ከተከሌሚካኤል አበበ

Next Story

በጎጃም ከሚያዝያ እስከ ነሐሴ ባሉት ወራት 8 አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፤ ሰማያዊ ፓርቲ ማብራሪያ ጠየቀ

Go toTop