በኦሮሚያ አድማው እየተቀጣጠለ ነው * ንብረትነቱ የአዜብ መስፍን ከሆነ መሬት የተሰበሰውን ቡና ሕዝብ እየተከፋፈለው ነው

August 23, 2017

(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች ለአምስት ቀናት የሚቆይ አድማ መጀመሩን ቀድም ሲል ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም:: አድማውን ለማስተጓጎል ሕወሓት የሚመራው መንግስት ሃይል ለመጠቀም ቢሞክርም ሕዝብ ግን ከዓላማው አልመለስም እንዳለ ነው::

አድማው እየተደረገባቸው ካለባቸው ከተሞች መካከል ጅማ ስትሆን በጅማ ዞን ሊሙ ኮሳ ወረዳ ውስጥ የሚገኘውና “ሆራይዘን ቡና” የተሰኘው ንብረትነቱ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ባለቤትነት ከሚተዳደረው ሁለትመቶ ሄክታር መሬት ላይ የተሰበሰበውን ቡና ሕዝቡ እየተከፋፈለው መሆኑን ከስፍራው የደረሱን መረጃዎች ጠቁመዋል::

የሕወሓት ባለስልጣናት በስማቸውም ሆነ በዘመዶቻቸው ስም በርካታ ንብረቶችን የያዙ ሲሆን ልክ ዶ/ር መረራ ጉዲና ከአስራ አምስት ዓመታት በፊት “የሚበላውን ያጣ ሕዝብ መሪዎቹን ይበላል” እንዳሉት ተቃውሞዎች ሲነሱ የነርሱ ንብረቶች ቅድሚያ ተጠቂ እንደሚሆኑ በተከታታይ ከሚደረጉ ሕዝባዊ አድማዎች ለማየት ችለናል::

Previous Story

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) አራተኛ ጉባዔውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀቀ

Next Story

የምሥራች! በጋሻው ደሳለኝ እግዚአብሔር ሆነ! – ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

Go toTop