ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አንዳርጋቸው ጽጌ የፊታችን እሁድ በቨርጂኒያ የሕዝብን ጥያቄ ይመልሳሉ

September 17, 2013

(ዘ-ሐበሻ) የግንቦት 7 ንቅናቄ አመራር የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እሁድ ሴፕቴምበር 22 ቀን 2003 በዋሽንግተን ዲሲ/ ቨርጂኒያ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለሕብረተሰቡ ገለጻ ለማድረግ ሕዝባዊ ስብሰባ መጥራታቸውን የመርሃ ግብሩ አዘጋጆች ለዘ-ሐበሻ በላኩት በራሪ ወረቀት አስታወቁ። “የወቅቱ የኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታና ለነፃነትና ለዴሞክራሲ የሚደረገው ትግል ላት ገለጻ ይደረጋል” በሚል በአርሊንግተን ቨርጂኒያ ከቀኑ 2 ሰዓት ጀምሮ የተጠራው ይኸው ሕዝባዊ የውይይት መድረክ ሰፊ የጥያቄና መልስ ክፍል ስለሚኖረው ማንኛውም ኢትዮጵያዊና ኢትዮጵያን ወዳጅ በመገኘት እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ለዚህ ሕዝባዊ ውይይት መድረክ የመጥሪያ በራሪ ወረቀት የሚከተለው ነው።

Previous Story

ለጥንቃቄ፦ ካድሬዎች በሞቫይል ስልክ እያደናበሩ ነው!

Next Story

በአዲስ አበባ ግብረሰዶም በአስደንጋጭ ፍጥነት እየተስፋፋ ነው!

Go toTop