«አንተስ…?»

February 6, 2017

( ወለላዬ )

ዓይኔን  በዓይኔ  ያየሁበት፣

በስተእርጅና  ያገኘሁት፣

የትናንቱ  ማሙዬ፣

ያሳደኩት  አዝዬ

የንግሊዞችን  ወረራ

ሰምቶ፣

በቴዎድሮስ ሞት

ተቆጥቶ፣

ለምን?  ለምን  ሞተ?

ብሎ  ሲያለቅስ፣

የዓይኑን  ዕንባ  ላደርቅ-

የልቡን  መሰበር  ላድስ፣

ጀግኖቻችንን  ቆጥሬ-

ታሪካችንን  ባወድስ፣

ዕንባውን  ዋጥ  አድርጎ-

በአትኩሮት  ዓይኔን  እያየኝ፣

«አንተስ…?» አንተስ!-

ምን  ሰርተሀል?  በማለት  ጠየቀኝ።

እድሜ  ቢደራረብ  ተግባር  ሳይላበስ፣

እንደዚህ  እንደኔ  ያስጠይቃል  ለካስ!

 

 

 

Previous Story

[ፓትርያርክ አቡነ ማትያስን] በማሸነፌ ተደስቻለሁ፣ በማሸነፌ አልተደሰትኩም !!

Next Story

ምጧ የተራዘመባት- ኢትዮጵያ! – ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

Go toTop