ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከእስር ሊፈታ ነው

September 30, 2016

(ዘ-ሐበሻ) በ2014 ኦክቶበር ወር ላይ ‹‹መንግስት ይገድላል፣ ያፍናል፣ ይጨቁናል” ብሎ ጽፏል; እንዲሁም በሌሎች ተጨማሪ 2 በተከሰሰባቸው 3 ክሶች የ3 ዓመት እስራት የተፈረደበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሊፈታ መሆኑ ተሰማ::

ከቤተሰቦቹ አካባቢ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለከተው ጋዜጠኛ ተመስገን የ እስር ጊዜውን ጨርሶ በአመክሮ ከ13 ቀን በኋላ ይፈታል::

ዓ.ም የመንግስትን ስም ማጥፋት፣ ህዝብን ማነሳሳትና የህዝብን አመለካከት ማናወጽ በሚሉ ሶስት ክሶች ጥፋተኛ ተብሎ የነበረው ተመስገን በተፈረደበት ወቅት አንዳችም የቅጣት ማቅለያ እንዳላቀረበ ይታወቃል::

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በ እስር ቤት ቆይታው የተለያዩ ስቃዮች ሲደርሱበት እንደነበር ዘ-ሐበሻ በተደጋጋሚ መዘገቧ አይዘነጋም::

Previous Story

የአንድ ሕዝብ አንድ ሀገር ድርጅት ምንድን ነው? አንዱዓለም ተፈራ

Next Story

ዩቱብ ኢንተርኔት በሌለባቸው ቦታዎች ቪዲዮዎችን መመልከት የሚያስችል ቴክኖሎጂ ይፋ አደረገ

Go toTop