ኦቦ ሌንጮ ለታ ተመላሽ ዲያስፖራ የመሆን መብቱ ለምን ተከለከለ?

ከአብሼ ገርባ

የዛሬ ስድስት ወር ገደማ ኦቦ ሌንጮ ያለኝ የፖለቲካ ሀሳብ ኢንቨስት ማድረግ እፈልጋለሁ ብሎ ጏዙን ጠቅልሎ ሀገር ቤት መግባቱ ይታወቃል:: ሆኖም በፍጥነት በመጣበት እግር ሀገሩን ለቆ እንዲወጣ ተደረገ::

የሌንጮ ለታን መባረርና አሁን ያለውን የዲያስፖራ ጥሪ ስንመለከት የተለየ የፖለቲካ ሀሳብ ኢንቨስት ማድረግ እንደማይፈቀድና ዶላርና ቦዶ ሀሳብ ብቻ ይዞ መምጣት እንደሚቻል ነው::

አንድ የኦሮሞ ዲያስፖራ በቴሌቪዥን መስኮት ቀርቦ በዚህ ሀገር ውስጥ አንድም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የለም ብሎ በአንድ ቀን አዳር የሰብዓዊ መብት ጥሰት አለመኖሩን ገምግሞ ምስክርነት መስጠት የሚችል ጭንቅላት ያለው ዲያስፖራንም ለማየት ችለናል::

ኢህአዴግ ፖለቲካውን መቶ በመቶ ዝግ በማድረግ ዶላሩን ብቻ አምጡ እያላቸው ነው::

ዋናው ቁልፉ ግን ሀገሪቱን አንቆ የያዘው የዶላር ችግር ሳይሆን ፖለቲካው ስለተቆለፈበት ነው::

በኔ ግምት የዲያስፖራ ዶላር አይደለም የአሜሪካ ዶላር ጠቅላላ ተሰብስቦ ቢመጣ የሀገራችን የፖለቲካ ችግር እስካልተፈታ መፍትሄ ሊሆን አይችልም:

Previous Story

የሀይማኖት መብታችን የሚከበረው በነፃነት ትግል ነው! – ሰማያዊ ፓርቲ

Next Story

የዋሺንግተን ዲሲ የጋራ ግብረሃይል “በሙስሊም ወንድሞቻችን ላይ የተፈረደው ፍርድ በ90 ሚሊዮን ሕዝብ ላይ የተፈረደ ፍርድ ነው” ሲል አወገዘ

Go toTop