በስልጢ ለሳምንት የዘለቀው ቃጠሎ በደን ላይ ውድመት አደረሰ

February 21, 2015

አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንደዘገበው
በደቡብ ክልል ስልጢ ዞን ስልጢ ወረዳ ውስጥ በተፈጥሮ ደን ላይ የእሳት ቃጠሎ ውድመት እየደረሰ መሆኑን ምንጮቻችን የጠቆሙ ሲሆን የወረዳው ግብርና ላይ በበኩሉ እሣቱ በቁጥጥር ስር መዋሉን ጠቅሶ የአደጋው መንስኤ በፖሊስ እየተጣራ ነው ብሏል፡፡

ከሳምንት በፊት የጀመረው የእሳት ቃጠሎ እስካለፈው ሐሙስ ድረስ አለመቆሙን የተናገሩት ምንጮች፤ ከወረዳው ዋና ከተማ ቂቢት በስተምዕራብ 5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በዘቢዳር ሰንሰለታማ ተራራ ላይ የሚገኘው ይሄው ደን፤ በአራት አቅጣጫዎች በእሳት እየወደመ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

እስካሁን እሳቱን ለማጥፋት ከአካባቢው መስተዳድር የተደረገ ጥረት አለመኖሩን የጠቆሙት ምንጮቻችን፤ በግምት ከ20 ሄክታር በላይ ደን ሳይቃጠል እንደማይቀር ተናግረዋል፡፡ ወሌ 26 እና ቦሌ በሚባሉ ቀበሌዎች ውስጥ የሚገኘው ደኑ፣ የአካባቢው የተፈጥሮ ሃብት መሆኑን የጠቀሱት ምንጮች፤ ከዚህ በፊትም በተደጋጋሚ ቃጠሎ እንደደረሰበትና ግለሰቦች ለማገዶ ፍጆታ ሲሉ እሳት ለቀውበት ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን ገልፀዋል፡፡

የወረዳው የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ መሃመድ ከድር ስለጉዳዩ ተጠይቀው ሲመልሱ፤ ከግብርና ቢሮና ከፖሊስ የተውጣጣ ግብረ ሃይል መሰማራቱንና እሳቱን በትናንትናው እለት መቆጣጠር መቻሉን ጠቅሰው ቃጠሎው በሰውና በንብረት ላይ ያደረሰው ጉዳት ባይኖረውም በደኑ ላይ ያደረሰው ውድመት መጠን እንዲሁም ፖሊስ የእሳቱን መንስኤ ፖሊስ እየመረመረ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

Previous Story

ተወዳድሮ ማሸነፍ የሚችለው ሰማያዊ ብቻ መሆኑ ተረጋገጠ

Next Story

Hiber Radio: ወይንሸት “ከምርጫው ተወዳዳሪ ዕጩነት እኔን እጣ አልደረሰሽም ብለው አስወጥተውኛል” ማለቷ… እቴጌ ጣይቱ በታሪክ ሲታወሱ የሚኖሩ ታላቅ ሴት (ልዩ ጥንቅር).. አበበ ገላው የሀሰት ዲግሪ የሰበሰቡ የስርዓቱ ሰዎችን የተመለከተ ሰሞኑን አዲስ መረጃ እንደሚያቀርብ ገለፀ… አገዛዙ በኢትዮጵያ በሙስሊም ወጣቶች ላይ የከፈተው የእስር ዘመቻ የድል ዋዜማ ጠቋሚ ነው መባሉና ሌሎችም

Go toTop