ዴቪድ ሞይስ ሰር አሌክስ ፈርጉሰንን ተኩ

May 10, 2013

አብርሃም አያሌው

ማንችስተር ዩናይትድ ስኮትላን ዳዊውን ዴቪድ ሞይስን የሰር አሌክስ ፈርጉሰን ምትክ አድርጐ ሰየመ።
የቢቢሲ ዘገባ እንዳ መለከተው የ50 ዓመቱ ዴቪድ ሞይስ እ.ኤ.አ ከሐምሌ 1 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ለስድስት ዓመታት ክለቡን እንዲያሰ ለጥኑ ተቀጥረዋል።
ሞይስ የኤቨርተን ክለብን እ.ኤ.አ ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ላለፋት 11 ዓመታት አሰልጥነዋል።
ያልተጠበቀውን ከአሠልጣኝነት የመሰናበት ዜና ከትናንት በስቲያ ይፋ ያደረጉት የ71 ዓመቱ ሰር አሌክስ «በዴቪድ ሞይስ ሁላችንም ያለልዩነት ተስማምተናል» ሲሉ ተናግረዋል።
«ዩናይትድን ሊያሰለጥን የሚገባው አንድ አሠልጣኝ ሊያሟላው የሚገባው ብቃት ሁሉ ከሞይስ ዘንድ አለ» ሲሉም ተሰናባቹ አሰልጣኝ አዲሱን የኦልድ ትራፎርድ መሪ አሞካ ሽተዋል።
በክለቡ ቦርድ የተሾ ሙት ሞይስ በበኩ ላቸው «ይህ ታላቅ ክብር ነው፤ ሻምፒዮን ቡድንን ለማሰል ጠን በታላቅ ሰው ተመ ራጭ መሆን ያስደ ስታል፤ ሥራው እንደሚ ከብድ አውቃለሁ ፤ ያም ሆኖ በሆነው ሁሉ ተደስ ቻለሁ» በማለት ሃሳባ ቸውን ገልጸዋል።
27 ለሚጠጉ ዓመታት ዩናይትድን ያሰለጠኑት ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ክለቡን ለ13 የፕሪሚየር ሊግ ፤ አምስት የኤፍ ኤ ካፕና ለሌሎችም ለበርካታ ዋንጫዎች ክበር አብቅተዋል።
ከመጪው የውድድር ዘመን ጀምሮም በክለቡ ዳይሬክተርነትና አምባሳደርነት እያገለገሉ በኦልድትራፎርድ እንደሚቆዩ ታውቋል።

Previous Story

በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ ሲያጠምቁ የከረሙት አነጋጋሪው መ/ር ግርማ ወንድሙ እንዳያጠምቁ ታገዱ

Next Story

ወያኔ ባለስልጣናቱን አቶ መላኩ ፈንታን እና ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስን አሠረ

Go toTop