ከሰሜን ጎንደር ጭልጋ ከተማ የደረሰኝ መረጃ 

April 24, 2014

ከጭልጋ ከተማ ርቃ የምትገኝ የገጠር ከተማ የሆነችው ጮንጮቅ በ15/08/2006 አ.ም በገበሬዎችና በፌድራል ፖሊሶች በተፈጠረ የትኩስ ልውውጥ የብዙ ሰዎች ህይወት ሲቀጠፍ ብዙዎችም በከባድና ቀላል ቁስለኛ ሆነዋል። የገበሬዎች ቁስለኛም ሆነ የሞተ ወደ ሆስፒታል የሚያደርሳቸው የለም። ከምሽቱ 4:33 እና 5:45 እንዲሁም 7:25 ሰአት … በእነዚህ ሰአቶች ባጠቃላይ 11 መኪኖች ቁስለኛ እና አስከሬን የ2 የጭነት አውሱ አስከሬን የጫኑ ሲሆን 5ቱ አንቡላንስና ከባድና ቀላል ቁስለኞች ይዘዋል። 4ቱ ደሞ አጃቢ የሆኑ የፌድራል ፓሊሶች ናቸው።ይህ በእንዲህ እንዳለ 4 አውሮፕላኖች በተደጋጋሚ በከተማውና በጫካው ሲመላለሱ ያደሩ ሲሆን ማክሰኞ እለት ማታ ከ4:00 ሰአት ጀምሮ ነው። እሁድ እለት ማታ 4 ፌድራል ፓሊሶች ተገለው አስከሬናቸው እንጅ መሳሪያቸው አልተገኘም። በዚሁ እለት 1 ኤሌኮፍተር በጭልጋ ከተማ በሰው ቁመት ሲያንጃብብ አድረዋል።

ሰሜን ጎንደር አከባቢ የምትገኙ ጓዶች ሁኔታውን አጣሩልን።

Previous Story

የናቁትን «አረዳ» ሊጎበኙ መጥተው  «አረዳ ጠባቂ» ብሎ ጠባቂውን መናቅ ምን ይሉት እውቀት ነው?

Next Story

[የሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ] – አንድነት ይመጣል፡ እውነቱም ይገለጣል (ከዲ/ኤፍሬም ስለሺ)

Go toTop