አቡነ ዘካሪያስ ካህናቱን ያወገዙበት ደብዳቤዎችን ይዘናል

ከአዘጋጁ፡ በሚኒሶታ ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ያለው ጉዳይን እየተከታተልን በስፋት የሚደርሱንን አስተያየቶች በማስተናገድ ላይ እንገኛለን። አንዳንድ የዘ-ሐበሻ ወዳጆች በገለልተኛው ወገን ያለውን ብቻ እያቀረባችሁ ነው፤ ይህ ደግሞ ሚዛናዊነታችሁን ሊያሳጣችሁ ይችላል ሲሉ አስተያየት ሰጥተውናል። ዘ-ሐበሻ እንደ ነፃ ሚዲያነቷ የሁሉንም ሃሳብ ታስተናግዳለች። የተላኩላትን አስተያየቶችን ዘ-ሐበሻ ሳታስተናገድ የቀረችባቸው ጊዜያት የሉም። ሆኖም ግን አንዳንዶች የዘ-ሐበሻን በር ሳያንኳኩና ለዘ-ሐበሻ ሳይጽፉ ዘ-ሐበሻን ሊወቅሱ ቢሞክሩ አስተያየታቸው ሚዛን አይደፋም። ልንወቀስ የሚገባው የተላከልንን ጽሁፍ አናወጣም ስንል ብቻ ነው። ዘ-ሐበሻ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አትገባም፤ ሆኖም ግን ዜና የሆኑ ነገሮችን ሁሉ ታስተናግዳለች። አሁንም ቢሆን በየትኛውም ቦታ አቋማቸውን ያደረጉ ሰዎች በድረገጻችን ሊገለገሉበት ይችላሉ። በግልጽ በዘ-ሐበሻ ኤዲቶሪያል ላይ እንደተቀመጠው በድረገጹ ላይ የሚቀርቡ አስተያየቶች ሁሉ የጸሐፊው እንጂ የዘ-ሐበሻ አቋሞች አይደሉም።

ለዛሬው አቡነ ዘካሪያስ ካህናቱን ያወገዙበትን ደብዳቤዎች ለግንዛቤ ይረዳ ዘንድ አስተናግደናል።

Previous Story

ምክር ለሰማያዊ ፓርቲ (በክፍያለው ገብረመድኅን)

Next Story

ኢትዮጵያን ለዘመናት የተቆራኛት ልክፍት፡ ከዓላማ ይልቅ ጥላቻን መሪ ያደረገ ፖለቲካ!

Go toTop