የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪቃል በደሴ የተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል

April 6, 2014
Millions of voices for freedom – UD

የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪቃል በደሴ የተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ በስፍራው የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ ከፍተና አመራሮችና የዞን አመራሮች በሰልፉ ለተሳተፈው የደሴ ህዝብ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ #Dese #UDJ “እድሜ ለአንድነት አስተነፈሰን” የደሴ ነዋሪ.  ይህ ሁሉ አልፎ ዛሬ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ በአስተዳደሩ ላይ በተለይም በመሬት ይዞታ ባለቤትነት ጉዳይ እና አላግባብ ስለታሰሩት ኢትዮጵያውያን ድምጹን ከፍ አድርጎ እያሰማ ይገኛል:: ሰላማዊ ሰልፉ እንደተጀመረ ፖሊስ መንገዱን በመዝጋት ሰልፈኛውን ለማወክ ጥረት አድርጎ ነበር:: ህዝቡ ግን ፖሊስን እየጣሰ ሰልፉን በሰላማዊ መንገድ እያደረገ ነው::

የደሴው ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ እየተካሔደ ቢሆንም የአዲስ አበባው ዋና ጽ/ቤት ከፍተኛ በሆነ የፖሊስ ሀይል ተከቧል፡፡

ተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከሚስተጋቡ መፈክሮች ውስጥ
– መሬት ለህዝብ ይመለስ
– ጭቆና በቃን
– ድል የህዝብ ነው
– በግፍ የታሰሩ ይፈቱ

– አንድነት ኃይል ነው
– የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ

 

Previous Story

በአማራ ክልል ከአምስት ሺህ በላይ ዜጎች ሜዳ ላይ ወድቀዋል ሰማንያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ወድመዋል በጀት ስለሌለን ምንም ያደረግነው የለም

Next Story

በስምምነት ላይ የተመሰረት ባህላዊ ውህደት Vs ህገ-መንግስታዊ ቀናዒነት ( ገለታው ዘለቄ )

Go toTop