በደሴ ፖሊስና የደህንነት ነን የሚሉ ግለሰቦች የሰላማዊ ሰልፉን ቅስቀሳ ለማደናቀፍ ያደረጉት ሙከራ ሳይሳካ ቀረ

April 5, 2014

April 5, 2014 8:00 am

የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ባልደረቦች ክስተቱን በፎቶግራፍ አንስተዋል

የአንድነት ከፍተኛ አመራሮችን ያካተተውን የቅስቀሳ ቡድን ተግባር ለማደናቀፍ ፖሊሶችና ደህንነት ነን የሚሉ ግለሰቦች በስውር ቪዲዮ በመቅረፅ እና ስለሙስሊሙ የመብት ጥያቄ የሚስተጋቡ መፈክሮችን ለማስቆም ሙከራ አድርገዋል፡፡ በተለይም የከተማዋ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊ ቅስቀሳው በተደረገባቸው ስፍራዎች በመገኘት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችን ለማስፈራራትና ከቅስቀሳ ቡድኑ አባል ላይ የቅስቀሳ ቁሳቁስ ለመንጠቅ ሲሞከር በዝምታ ተመልክተዋል፡፡ ይህ ሁሉ የማደናቀፍ ሙከራ ቢደረግም ቅስቀሳው ተጠናክሮ ቀጥሏል፤  የደሴ ህዝብ ከአንድነት ፓርቲ ጎን በመሆን ቅስቀሳውን አጧጡፎታል፡፡

 

 

Previous Story

ህወሓት በአፅቢ (እንዳስላሴ) ረብሻ ለመቀስቀስ እየሞከረ ነው፤ ነገ እሁድ አረና ለጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ቅስቀሳውን ቀጥሏል

Next Story

ትንሽ ምላጭ አገር ትላጭ! (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

Go toTop