ስለሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ አመሠራረትና አሁን ያለበት ሁኔታ ምናልባት እስካሁን ያልሰማናቸው ጉዳዮች – (ልዩ ጥንቅር ከኢትዮጵያ ድምጽ ራድዮ)

March 12, 2014

“ቦርዱ በአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ ምእመናኑን ሰብስቦ ምእመናኑን ምንድን ነው የምትፈልጉት ሊለው ይገባል” – አጥናፉ
“ቤተክርስቲያኑ ሲመሰረት፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሴ በቋንቋችን ሥሰማ በደስታ ብዛት አልቅሻለሁ” ሰዊት
“ቤተክርስቲያኑ ገለልተኛ ነው ተብዬ አምኜበት ነው የገባሁት፤ ሃገር ቤት ይግባ የምል ከሆነ ጥዬ መውጣት እንጂ አሁን ተነስቼ ልበጥብጥ ማለት አይገባም ” – አበራ
“ሁሉንም ወገኖች ለማነጋገር እንፈልጋለን” አህመድ


የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ እስካሁን የተረጋጋ ሁኔታ የለም። ይህን ተከትሎ ከሚኒሶታ አልፎ በመላው ዓለም መነጋጋሪያ የሆነ ጉዳይ ሆኗል። በርካታ ሕዝብ፣ የኢትዮጵያ ኮምዩኒቲን ጨምሮ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ ሕዝብ የቤተክርስቲያኑን ቀጣይ እጣ ፈንታ እንዲወስን ቢጠይቁም ቦርዱ እስካሁን ምላሽ የሰጠው ምላሽ አለመኖሩ አነጋጋሪ ሆኗል። አባቶችም ሁለቱንም ወገኖች ለማስማማት ጥረት አላደረጉም በሚል በም እመናኑ ወቀሳ እየደረሰባቸው ይገኛል። ይህ እንዳለ ሆኖ በሚኒሶታ ዘወትር እሁድ የሚሰራጨው የኢትዮጵያ ድምጽ ራድዮ በዚህ ትልቅ ቤተክርስቲያን ዙሪያ ሰፊ ዘገባ አቅርቧል። ምናልባት እስካሁን ሰምተናቸው የማናውቃቸው ጉዳዮች ተነስተዋል። ብታደምጡት ትጠቀማላችሁ ብለን እናስባለን።

Previous Story

የአውሮፓ ሕብረት በአዲስ አበባ መንግስትን እና ተቃዋሚዎችን እያነጋገረ ነው

Next Story

የብርሃኑ ዳምጤ (አባመላ) ቅልቅል (ከክንፉ አሰፋ) ጋዜጠኛ

Go toTop