ከለባን ከተማን ወደ ትግራይ ክልል ለማካለል የተነሳውን እቅድ በመቃወም በአፋር ከፍተኛ ንቅናቄ ተጀመረ

March 11, 2014

(ፎቶ ፋይል)
በአፋር ክልል የምትገኘው በወርቅ እና በፖታሺየም እንዲሁም በተለያዩ ማእድናት የበለጸገችውን የኮለባን ከተማን ወደ ትግራይ ክልል ለማካለል የሕወሓት መራሹ መንግስት እርምጃ ለመውስድ በአካባቢው መገኘቱን ተከትሎ ከተማዋ በአፋር ተወላጆች ከፍተኛ ተቃውሞ እየታመሰች መሆኑን የዜና ምንጮችን ጠቅሶ ምኒልክ ሳልሳዊ ዘግቧል። እንደ ዘገባዎቹ ከሆነ ከትላንትና ቀትር ጀምሮ የተነሳው ተቃውሞ የአፋር ህዝብ በቦታው በመገኘት ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመሆን ከባድ መሳሪያ ከታጠቁ የሕወሓት ወታደሮች እና የፈደራል ፖሊስ አባላት ጋር ፊት ለፊት በመፋጠጥ መሬታችን “ከትግራይ አይቀላቀልም፤ አናስነካም” በሚል ከፍተኛ ተቃውሞ በማድረግ ላይ ነው።

ዝርዝር መረጃ እንደደረሰን እንመለሳለን።

Previous Story

ኃይለማርያም ደሳለኝ በዳንስ ላይ (ዜና ፎቶ)

Next Story

ሞት የስብሐት ነጋ በርን እያንኳኳ ነው (ሁኔ አቢሲኒያዊ ከፒተርቦሮው ዩ.ኬ)

Go toTop