“ከማጥናት በቀር ሌላ ነገር የማያውቁ፤ የተስተካከሉ ልጆች ነው ያሉን” – ከኃይለመድህን አበራ እናት ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ!!

February 24, 2014

ረዳት አብራሪ ኃይለመድህን አበራ ባለፈው ሳምንት፤ ሲያበር የነበረውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ጄኔቭ ማሳረፉ የሚታወስ ነው። ከአብራሪው ጋር በተያያዘ እስካሁን እህቱ እና መንድሙ የየራሳቸውን ሃሳብ እና አስተያየት ሰጥተዋል። አሁን ደግሞ ከ እናታቸው ጋር የተደረገውን ቃለ ምልልስ ይዘን እንቀርባለን። ቃለ ምልልሱን በድምጽ ያደረገው ዳዊት ሰለሞን ነው። ባህርዳር ላይ የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ ለማስተባበር በስፍራው ተገኝቶ ነበር። እናም ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ቃለ ምልልስ አድርጎላቸዋል። በመግቢያውም ላይ እንዲህ የሚል ማስታወሻ ጽፏል። “በባህርዳር ቆይታዬ ከሰሞኑ ዋነኛ የመነጋገሪያ ርዕስ ከሆነው ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ ወላጅ እናት ጋር ለጥቂት ደቂቃዎች የመገናኘት እድል ተፈጥሮልኝ ነበር፡፡ እናትየው የወንድማቸውን አርባ አውጥተው ከሩቅ ቦታ መመለሳቸው በመሆኑ ድካም ቢነበብባቸውም ለማቀርብላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት አላመነቱም፡፡ ምስጋናዬን እያቀረብኩ ልጃቸውን የተመለከተ መልካም ዜና እንዲያደምጡ ጸሎቴ ነው::” ብሏል።

ቃለ ምልልሱን ያደረገው – ዳዊት ሰለሞን
ወደ ጽሁፍ የመለሰው – ዳዊት ከበደ ወየሳ

ቃለምልልሱን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

Previous Story

ረዳት ፓይለቱ ኃይለመድህን አበራን በመደገፍ በስዊዘርላንድ ሰላማዊ ሰልፍ ተጠራ

Next Story

በቦሌ የባንክ ጥበቃው ለጥበቃ በተሰጠው ጠመንጃ ራሱን በጥይት መትቶ ገደለ

Go toTop