የኢትዮጵያ መንግስት በእስር ላይ የሚገኙ ግለሰቦችን ክስ አቋርጦ እንዲፈቱ ውሳኔ ያሳለፈው “ኢትዮጵያን በጠንካራ አለት ላይ ለማኖር፣ ጠላቶቿን ለመቀነስ እና ጉልበት ለመሰብሰብ” መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። “ጉዳዩን እኛም መጀመሪያ ስንሰማው” አስደንግጦናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ሆኖም ውሳኔው “ለኢትዮጵያ የሚበጅ፣ ዘላቂ ጥቅም የሚያግዝ፣ በአውደ ውጊያ የተገኘውን ድል በሰላሙ መድረክ እንዲደገም የሚያደርግ” በመሆኑ “እየመረረን የዋጥነው እውነት ነው” ብለዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
[በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃዎች ይታከሉበታል]