አርቲስት ታማኝ በየነን ጨምሮ ታዋቂ ግለሰቦች እና የቀድሞ ጦር ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች ወደ ግንባር ዘመቱ

November 26, 2021
 አርቲስት ታማኝ በየነ እና ፖለቲከኛ አንዳርጋቸው ፅጌ ጨምሮ ታዋቂ ግለሰቦች እና የቀድሞ ጦር ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች ወደ ግንባር ዘመቱ።
ፖለቲከኛ ነዓምን ዘለቀ እና ብርጋዴር ጀነራል ካሳዬ ጨመዳም ወደ ግንባር ከዘመቱት መካከል ይገኙበታል።
በኢትዮጵያ ያጋጠመውን የህልውና ዘመቻ በተለያየ መንገድ ከፊት ሆነው ሲታገሉ የነበሩ አርቲስቶች እና የቀድሞ ሠራዊት የጦር አመራሮች የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ወደ ግንባር መዝመትን ተከትሎ እነሱም እንደሚዘምቱ ከዚህ ቀደም ቃል ገብተው ነበር።
በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ ያጋጠማትን የህልውና አደጋ ለመመከት ዛሬ ወደ ግንባር መዝመታቸውን ኢብኮ ዘግቧል።
ሕዳር 17/2014 ዓ.ም (አሚኮ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

“ካሳጊታ በመከላከያ ሰራዊት እጅ ገባች” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከጦር ግንባር

Next Story

“ወደ ተከዜ ግንባር የዘመትኩት የሀገር መከላከያ ሠራዊት ተጋድሎን ለመቀላቀል ነው” ረዳት ፕሮፌሰር አማረ ጥጋቡ

Go toTop