ፕ/ር መረራ እና አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮምያ ጊዚያዊ የሽግግር መንግስት መስርተናል አሉ – ፋሲል የኔአለም

July 2, 2021
እቅዳቸው መንግስትን በህዝባዊ አመጽ ማዳከምና ለህወሃት አቀባበል ዝግጅት ማድረግ ይመስላል። ይህ እቅድ መስከረም 30 ላይ አልሰራም ነበር። አሁን ደግሞ ህወሃት ጉልበት ያገኘ መስሏቸው እንደገና ይዘውት ብቅ ብለዋል።
ኢትዮጵያን አፍርሶ እንጨቷን ለመሞቅ የሚደረገው ሩጫ ከማራቶን ወደ 5 ሺ ሜትር ተቀይሯል።
በዚህ ፈታኝ ጊዜ ለአገር አንድነት በጋራ እንደመቆም፣ ” ጊዚያዊ መንግስት አቋቁሜያለሁ” እያሉ በአመጽ ጫና ለመፍጠር መሞከር በታሪክ ፊት ያስጠይቃል። ይህም ጊዜ ያልፋል። ኢትዮጵያም ትቀጥላለች።
እስከዛሬ ያልተመለሰልኝ አንድ እንቆቅልሽ አለ። እባካችሁ የስነ ልቦና ባለሙያዎች እርዱኝ። በህወሃት ሲሳደዱ የነበሩ ሰዎች አሳዳጃቸውን መልሰው የሚናፍቁበት ሚስጢር ምንድን ነው?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የአለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ዳግም እንዳይመረጡ ተጠየቀ

Next Story

ሃቅ መስዋዕትነት ከተራራ ይልቅ ትከብዳለች፣ የሸረኛ ሞት ከላባም ትቀላለች! – ሚኪ

Go toTop