19 ኤርትራዊያን ኬንያ ውስጥ ታሰሩ

February 21, 2019

 

በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር የተጠረጠሩት 19 ኤርትራዊያን በዛሬው እለት ፍርድ ቤት መቅረባቸውን የኬንያ ጋዜጦች ዘገቡ፡፡ እንደመረጃው ከሆነ ተጠርጣሪዎቹ በፕራዶ መኪና የኬንያን ሞያሌ ከተማ ሊያቋርጡ ሲሉ የተያዙት ባለፈው ሳምንት ነበር፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=9K1EwuewSOA

ከኢትዮጵያ ተነስተው የኬንያን ድንበር ሲያቋርጡ የተያዙት እነዚህ ተጠርጣሪዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ክስ ስለቀረበባቸው ጠፍተው እየሄዱ መሆኑን ገልፀው እቅዳቸውም ዩኔንኤችሲአር ጥገኝነት መጠየቅ እንደነበር ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ዋስትና ሳይፈቅድላቸው ጉዳዩን ለሚቀጥለው ወር ቀጥሮታል፡፡

Previous Story

የጎንደር ሕብረት ለጎንደር ተፈናቃዮች አንድ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር መመደቡን አስታወቀ

Next Story

የጉራጌ ህዝባዊ ንቅናቄ(ጉህን) በዛሬው እለት መግለጫ አውጥቷል

Go toTop