የህዳሴው ግድብ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ለቻይናዊያን ተሰጠ

February 20, 2019

ስራው የቆመውን የህዳሴ ግድብ ግንባታ ለማስቀጠል የኢትዮጵያ መንግስት ስራውን ሙሉ በሙሉ ለቻይናዊያን መስጠቱ ታወቀ፡፡ የግድቡን ግንባታ በተመለከተ ከሁለት የቻይና ኩባንያዎች ጋር ስምምነት ተፈፀመ፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=SvwytfrDZTg&t=73s

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በትላንትናው እለት የተፈራረመው ስምምነት40 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ መሆኑን ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡ ሲጂጂሲ CGGC የተባለው የቻይናው ኩባንያ ግድቡ በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2020 ስራ እንዲጀምር የሚያስችሉ ግንባታዎችንና ሌሎች ስራዎችን እንደሚያከናውን ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አብርሀም በላይ በስምምነቱ ወቅት ሲናገሩ ‹‹ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ለማድረግ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በመጣመር ይሰራል ተብሎ ይጠበቃል›› ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም የግድቡን የኤሌክትሪካል፣ ሜካኒካልና ስትራክቸራል ስራዎችን እንዲያከናውን በ113 ሚሊዮን ዶላር ቮይዝ ሀይድሮ ሻንጋይ ከተሰኘው የቻይና ተቋም ጋር ስምምነት መደገሩ ይታወሳል፡፡

Previous Story

በ1997 ዓ.ም. የተደረገውን ሀገራዊ ምርጫ ተከትሎ የተፈጠረው ፖለቲካዊ ቀውስና የህዝብ ጭፍጨፋ በባለሙያ ተጠንቶ በመፅሀፍ መልክ እንዲቀመጥ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀመረ

Next Story

በረቀቀ መንገድ ተደብቆ ወደ አዲስ አበባ የገባ 4 መትረዬስ ጠብመንጃ እና ከ46 ሺ በላይ ጥይት መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሸን አስታወቀ

Go toTop