ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከታሰረበት ዝዋይ እስር ቤት የለም መባሉ ቤተሰቦቹን ግራ አጋብቷል

December 9, 2016

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ያለ ታስሮ ከሚገኝበት ዝዋይ እስር ቤት ለጥየቃ የሄደ ወንድሙ ሊያገኘው አለመቻሉና የእስር ቤቱ ሀላፊዎችም ተመስገን እዚህ የለም በማለታቸው ቤተሰቡ ግራ መጋባቱን ያለበትን ሁኔታ አሳሪዎቹ እንዲአሳውቁ ጥሪ አድርገዋል።

ከህዳር 28 ቀን 2009 ዓመተ ምህረት ጀምሮ ላለፉት ሁለት ቀናት ጋዜጠኛ ተመስገኝ ደሳለኝ ታስሮ የሚገኝበትን የዝዋይ እስር ቤት ቢጠይቁም ተመስገን የለም ሲሉ የእስር ቤቱ ሹሞች ግቢውን ለቀው እንዲወጡ ማዘዛቸውን የጋዜጠና ተመስገን ደሳለኝ ወንድም በገጹ ይፋ አድርጓል።

ቤተሰቦቹ ዝወይ የለም የተባለውን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የት እንዳለ ለማወቅ ቃሊቲና ቅሊንጦ ቢፈልጉም ሊያገኙት ባለመቻላቸው መንግስት የት እንዳደረገው እንዲያሳውቅ ወንድሙ ጠይቋል።

ጋዜጠና ተመስገን ደሳለኝ በዝዋይ እስር ቤት ሕክምና ተከልክሎ፣በተደጋጋሚ ጠያቂም እየተከለከለ በስቃይ ውስጥ የቆየ ሲሆን በታሰረበት የፈጠራ የፕሬስ ክስ ሳቢያ የተፈረደበትን በአመክሮ ቢጨርስም ሳይፈታ መቅረቱ ይታወሳል።

Previous Story

70 ተማሪዎችን የያዘ የተማሪዎች ሰርቪስ ቦሌ ሰሚት ድልድይ ላይ ተገለበጠ

Next Story

የጥንታዌት ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አጭር ታሪክና ሥርዓት -bታሪኩ ዉነህ ጌታነህ

Go toTop