ጎንደር ለሪፈር አንልክም የተባለች ወልቃይቴ ህይወቷ አለፈ

March 29, 2016

ሙሉቀን ተስፋው

የወልቃይት ነዋሪ የሆነችው የ30 ዓመቷ ወላድ እናት በኹመራ ሆስፒታል በ19/07/08 የቀዶ ጥገና ህክምና ተደርጎላት በሰላም ከተገላገለች በኋላ ተጨማሪ ህክምና የሚያስፈልጋት በመሆኑ የሆስፒታሉ ሐኪሞች የተሻለ ህክምና እንድታገኝ ወደ መቀሌ እንድትሄድ ሪፈር ሊጽፉላት ይዘጋጃሉ፡፡

በኹመራ ሆስፒታል የነበሩ የእንኩየውሽ ገሌ ቤተሰቦች ወደ መቀሌ ሳይሆን ወደ ጎንደር ሆስፒታል መውሰድ እንደሚፈልጉ በመግለጽ ዶክተሮቹን ለጎንደር ሆስፒታል ይጽፉላቸው ዘንድ ይማጸናሉ፡፡ነገር ግን የካህሳይ አበራ ሆስፒታል ዶክተሮች የተጠየቁትን ለማድረግ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ሶስት ቀናትን ‹‹ለጎንደር ሆስፒታል አንጽፍም ››በማለት ያባክናሉ፡፡

ከሶስት ቀናት ጭካኔ በኋላ ህመምተኛዋ እየተዳከመች መምጣቷን የተመለከቱት ዶክተሮች ለጎንደር ሆስፒታል ሪፈር ይጽፋሉ፡፡እንኩየውሽ ጎንደር ሆስፒታል በደረሰች በሁለት ሰዓታት ልዩነት ውስጥም ህይወቷ በማለፉ ይህችን አለም ተሰናብታለች፡፡

ሙሉቀን ተስፋው

Previous Story

የወያኔ ባለስልጥኖች ከራሳቸው ባሻገር ለየትኛም ጎሳ ዘላቂ ጥቅም አልቆሙም

Next Story

‹ሀገር ማለት ሰው ነው›፤ እስኪ ሙት በለኝ! (በዲያቆን ዳንሄል ክብረት)

Go toTop