የሕወሓት አስተዳደር የመከላከያ ሰራዊት ለአባይ ግድብ መስሪያ ገንዘብ አናዋጣም አሉ

September 9, 2015

የወያኔ ኢህአዴግ ስርአት መከላከያ ሰራዊት ለአባይ ግድብ መስሪያ ገንዘብ እንዲያዋጡ ለቀረበላቸው ጥሪ እንዳልተቀበሉት የትህዴን ድምጽ ምንጮች ከመከላከያ ውስጥ ገለፁ::
Photo File
በምንጮቹ መረጃ መሰረት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እንደ አዲስ ለአባይ ግድብ መስሪያ የሚሆን በሚል ገንዘብ እንዲያዋጡ በአመራሮቻቸው ለቀረበላቸው ጥሪ አንቀበልም ማለታቸውን የገለፀው መረጃው ለቀረበው ጥሪ ሳይቀበሉት የቀሩበት ምክንያትም “ ባለፉት ጊዚያት በተደጋጋሚ የከፈልነውን ገንዘብ ቦንድ ይሰጣቸኋል ተብለን እስከ አሁን ድረስ ግን ሳይተገበር አንከፍልም” እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል::

መረጃው በማከል።- የሰራዊቱ ከፍተኛ አዛዦች በሰራዊቱ ውስጥ አጋጥሞ ያለውን ለአባይ ግድብ ገንዘብ አንከፍልም የማለቱ የመበታተን አደጋ። እንዴት አድርገን ለሰራዊቱ እናሳምነው በሚል በከባድ ውጥረት እንደሚገኙ የተገኘው መረጃ ጨምሮ አስረድቷል ሲል የትህዴን ድምጽ ዜናውን ቋጭቷል::

Previous Story

የሕወሓት መንግስት የታጠቁ ኃይሎቹን እና ካድሬዎቹን በማሰማራት በአርማጭሆ ሕዝብ ላይ ሰቆቃ እየፈጸመበት እንደሚገኝ ተዘገበ

Next Story

ችግሩ ወያኔን በማስወገድ ብቻ የሚፈታ አይደለም ! – ካለፈው የቀጠለ

Go toTop