Español

The title is "Le Bon Usage".

ፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የሌባ ተባባሪነት ለመደባቸው

June 23, 2013

ከጥቂት ሳምንታት በፊት ዘ-ሐበሻ የጥንታዊት ኢትዮጵያ አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ሊቀትጉሃን አስታጥቄ አባተ አቅመ ደካማ ለሆኑ አባት አርበኞች የፈቀዱላቸውን 25 ኮንዶሚኒየም ቤቶች ለግል ጥቅም አውለዋል፣ ከሚያከራዩዋቸው ሕንፃዎች ከሚያገኙት ገቢ ላይ የአከራይ ተከራይ ግብር አለመክፈል፣ ያላግባብ ወጪ ማድረግና በመሳሰሉት ተጠርጥረው መከሰሳቸውን መዘገቧ ይታወሳል። ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ታትሞ የወጣው ሪፖርተር ጋዜጣ “ፕሬዚዳንት ግርማ የአርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ክስ እንዲቋረጥ ጥሪ ማቅረባቸውን” ያትታል። ዜናውን ለተመለከተ ከዘራፊው የወያኔ ስርዓት ጋር በመተባበር “አበባ የመትከልና አበባ የመቁረጥ ስልጣን” ብቻ ተሰጥቷቸው ቁጭ ያሉት ፕሬዚዳንቱ እኚህን በርከት ያሉ አርበኞች አባቶችን ያስለቀሱትን ሊቀትጉሃንን ክሳቸው ተቋርጦ ይፈቱ ሲሉ በድፍረት መጠየቃቸው የሌባ ተባባሪነቱ ለመደባቸው፤ ወይም ከሌባ ጋር መተባበር ሱስ ሆነባቸው እንዴ? ያስብላል። የሪፖርተር ዜና እንደሚከተለው ነው። አንብቡትና ትዝብታችሁን ጣሉበት።

በከባድ የማታለል ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው የጥንታዊት ኢትዮጵያ አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት፣ ዋና ጸሐፊና የአስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ፣ የተከሰሱበት ክስ እንዲቋረጥላቸው ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፣ ለፍትሕ ሚኒስቴር የጻፉት ደብዳቤ ውድቅ መደረጉን ምንጮች ለሪፖርተር አረጋገጡ፡፡

የአርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ ለፕሬዚዳንት ግርማ በጻፉላቸው የመማፀኛ ደብዳቤ አማካይነት፣ ክሳቸው እንዲቋረጥላቸው ወይም በይቅርታ እንዲታለፉ ፕሬዚዳንቱ ደብዳቤውን የጻፉት በፍትሕ ሚኒስቴር የሕግና አስተዳደር ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ለአቶ ብርሃኑ ፀጋዬ መሆኑን ምንጮቹ አረጋግጠዋል፡፡

በከባድ የማታለል ወንጀል ተጠርጥረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ስምንተኛ ወንጀል ችሎት ክስ የቀረበባቸው የኢትዮጵያ አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ፣ ዋና ጸሐፊው ፲ አለቃ ሰጥአርጌ አያሌውና የአስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ አቶ በቀለ ሻረው መሆናቸው ይታወሳል፡፡

ፕሬዚዳንት ግርማ ተጠርጣሪዎቹ በአገራቸው የጀግንነት ታሪክ ከፍተኛ ቦታ እንዳላቸው፣ ለአገር ልማትም በአሁኑ ጊዜ ከፍተኛ እገዛ እያደረጉ መሆናቸውንና ዕድሜያቸውም የገፋ መሆኑን በመግለጽ፣ መንግሥት ይቅርታ አድርጐላቸው ክሳቸው እንዲቋረጥ በደብዳቤ መጠየቃቸውን ምንጮች አስረድተዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ ግንቦት 29 ቀን 2005 ዓ.ም. በቁጥር መ/818/2005 የጻፉትን ደብዳቤ የተመለከቱት የፍትሕ ሚኒስቴር ባለሥልጣናት ጥያቄው ተገቢ አለመሆኑን፣ ግለሰቦቹም የተጠረጠሩበትን የወንጀል ድርጊት ፍርድ ቤት ቀርበው በሚደረግ የግራ ቀኝ ክርክርና የሕግ ሒደት ብቻ የሚታይ መሆኑን በመግለጽ፣ ጥያቄውን ውድቅ እንዳደረጉት ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

እነ ሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ አባተ የተጠረጠሩበት ወንጀል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የነበሩት አቶ አርከበ ዕቁባይ፣ አቅመ ደካማ ለሆኑ አባት አርበኞች የፈቀዱላቸውን 25 ኮንዶሚኒየም ቤቶች ለግል ጥቅም አውለዋል፣ ከሚያከራዩዋቸው ሕንፃዎች ከሚያገኙት ገቢ ላይ የአከራይ ተከራይ ግብር አለመክፈል፣ ያላግባብ ወጪ ማድረግና በመሳሰሉት ተጠርጥረው መከሰሳቸውን፣ ዋና ጸሐፊውና የአስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊው እያንዳንዳቸው በ25 ሺሕ ብር ዋስ መለቀቃቸውንና ፕሬዚዳንቱ ባለመቅረባቸው ታስረው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ መሰጠቱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ (ሪፖርተር)

Previous Story

“የሙስሊሙን አቋም ወክለው የሚናገሩት የታሰሩት የእኔ ደንበኞች ናቸው” አቶ ተማም አባቡልጉ

Next Story

በቤተልሄም የወሲብ ጉዳይ ‹‹ዴሞክራት›› ለመባል የፈለጉት አቶ አብርሃም ደስታ

Zehabesha | Ethiopian Latest News, Top Analysis & Best Articles <h1 style="text-align:center">tHE HABESHA Ethiopian Reliable News Source – Truth Will Win</h1><title> <title><h2 style="text-align:left">Get the Best Scholarly Articles and Analysis on ZeHabesha</h2><title> <title><h3 style="text-align:right">Zehabesha Ethiopian News</h3><title> <title><h4 style="text-align:justify">Ethiopian Lates News</h4><title> <meta name="keywords" content="Ethiopian News, Ethiopia News, Ethiopian News Today, Top Stories, The Habesha, Latest News, Ethiopia, Breaking News, zehabesha, zehabesha Amharic News, The Habesha News, Headlines, borkena. bbc amharic, repoter, mereja, Ethiopian News provider"> <!-- Google Tag Manager --> <script>(function(w,d,s,l,i){w[l]=w[l]||[];w[l].push({'gtm.start': new Date().getTime(),event:'gtm.js'});var f=d.getElementsByTagName(s)[0], j=d.createElement(s),dl=l!='dataLayer'?'&l='+l:'';j.async=true;j.src= 'https://www.googletagmanager.com/gtm.js?id='+i+dl;f.parentNode.insertBefore(j,f); })(window,document,'script','dataLayer','GTM-5WDL6STX');</script> <!-- End Google Tag Manager --> <!-- Google tag (gtag.js) --> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=G-W9E3TWE2TL"></script> <script> window.dataLayer = window.dataLayer || []; function gtag(){dataLayer.push(arguments);} gtag('js', new Date()); gtag('config', 'G-W9E3TWE2TL'); </script> <meta name="msvalidate.01" content="4781C31A916C7AB883D8AF1F4F3BFC49" /> <link rel="icon" href="/path/to/favicon.ico"> <link rel="icon" type="image/png" href="/thehabesha.com/favicon-96x96.png" sizes="96x96" /> <link rel="icon" type="image/svg+xml" href="/thehabesha.com/favicon.svg" /> <link rel="shortcut icon" href="/thehabesha.com/favicon.ico" /> <link rel="apple-touch-icon" sizes="180x180" href="/thehabesha.com/apple-touch-icon.png" /> <link rel="manifest" href="/thehabesha.com/site.webmanifest" /> <meta name="seobility" content="48b995a16caf3ab9d546a000c18b65d3"> <main> <!-- Main content of your page goes here --> </main> <script type="text/javascript" src="//cdn.rlets.com/capture_configs/d2b/aac/e54/1fc4f7ea32cf1e1d818a0f2.js" async="async"></script> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=TAG_ID"></script> <script src="https://www.googleoptimize.com/optimize.js?id=OPT-M8Z33GL"></script> <meta name="google-site-verification" content="Lf_65x5pXGn-W1TA8CsfJi-53aAyIKdfVyM_QkwpvgY" /> <head> <title>Ethiopian Latest News: Top Analysis and the best Articles<title> <script defer data-domain="thehabesha.com/mEUHSv" src="https://api.publytics.net/js/script.manual.min.js"></script> <script> window.publytics = window.publytics || function() { (window.publytics.q = window.publytics.q || []).push(arguments) }; publytics('pageview'); </script> <!-- Google tag (gtag.js) --> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=UA-215686007-9"></script> <script> window.dataLayer = window.dataLayer || []; function gtag(){dataLayer.push(arguments);} gtag('js', new Date()); gtag('config', 'UA-215686007-9'); </script> <script async src="https://pagead2.googlesyndication.com/pagead/js/adsbygoogle.js?client=ca-pub-9091845805741569" crossorigin="anonymous"></script> <script async custom-element="amp-ad" src="https://cdn.ampproject.org/v0/amp-ad-0.1.js"></script> <title>Zehabesha Ethiopian Reliable News Source – Truth Will Win