ከ40 በላይ የሚሆኑ የአየር ኃይል አባላት ስርዓቱን ከድተው አርበኞች ግንቦት 7ን ተቀላቀሉ

July 31, 2015
Photo File

አርበኞች ግንቦት 7 እንደገለጸው በህወሓት አገዛዝ ስር የሚገኘው አየር ኃይል ከዚህቀደም የተንሰራፋው ዘረኝነት፣ ገደብ የሌለው ዘረፋ እና አስተዳደራዊ ግፍና በደል ያንገሸገሻቸው በርካታ አባላቱ ተዋጊ ጀቶችን እና ተዋጊ ሄሊኮፕተሮችን እየያዙ በተደጋጋሚ መክዳታቸው ይታወቃል፡፡ በአየር ኃይሉ ውስጥ የአባላት ኩብለላ ከምድር ኃይሉ በከፋ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሰሞኑን ደግሞ ከ40 በላይ የሚሆኑ ሞያተኛ አባላቱ ባንድ ጊዜ ከየምድቦቻቸው ተሰውረዋል፡፡

ስርዓቱን ከከዱት 40 ሞያተኛ የሆኑ የአየር ኃይሉ አባላት ውስጥ አብራሪዎች፣ ቴክኒሻኖች፣ የኮማንድ ፖስት እና የጠቅላይ መምሪያው ሰራተኞች ይገኙበታል፡፡ ቴክኒሻኖች ቁጥራቸው 15 ሲሆን ምድቦቻቸው ትራንስፖርት ሄሊኮፕተር ስኳድሮን፣ ሱ 27 ስኳድሮን እና አንቶኖቭ 12 ነበሩ፡፡

ከአየር ኃይል በየጊዜው ከሚከዱት ሞያተኞች ውስጥ የኤም.አይ 35 ተዋጊ ሄሊኮፕተር ስኳድሮን አዛዥ ሻለቃ አክሊሉ መዘነን ጨምሮ አብዛኞቹ ወደ በረሃ ወርደው አርበኞች ግንቦት ሰባትን ተቀላቅለዋል፡፡

Previous Story

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) ሶስተኛ ጉባዔ ተከናወነ

Next Story

በኢትዮጵያ እውነትና ፍትህ ከትቢያ የተሻለ ቦታ ቢኖራቸው ኖሮ….   አንዷለም አራጌ

Go toTop