በአፋር ክልል ወጣቶች ለውትድርና በግዴታ እየታፈሱ ነው

July 7, 2015

(ፎቶ ፋይል)ከአኩ ኢብን አፋር

በአፋር ክልል የህዝባዊ ወያነ ሐሪነት ትግራይ መንግስት የአፋር ህዝብን ደካማ ጎኑን በመጠቀም ወጣቶችን ለውትድርና እያፈሰ ይገኛል።

አለም አቀፍ የምግብ ተረድዖ ድሪጅት በእንግለዘኛ ምህጻሩ WFP ( worlid food program ) ለኢትዮጲያ ህዝብ የሚሰጠው የእርዳታ እህል ለውትድር መደልያ በመጠቀም በአፈር ክልል በብዙ ወረዳዎች እርዳታን ለማገኘት ከአንድ አባወራ ቢያንስ አንድ ሰው ለውትርና መመዝግብ አለበት።

የወያነ መንግስት የመዕራባዊያን ድጋፍ ላለማጣት የገዛ ወታደሮቹን በሰላም አስከባሪነት ሽፋን በሶማሊያ እና በደርፎር በማሰማራት እየፈጃቸው መሆኑን የሚታወቅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት አፈሳው እየተካሄደ ይገኛል።

በአፋር ክልል 80% የሚሆን ህዝብ ከውጭ በሚገኘው እርዳታ የሚተዳደር ሲሆን ወያነ ይህን ደካማ ጎናቸውን በመጠቀም እርዳታ ለማገኘት አንድ ሰው ከአንድ አባወራ ለውትድሪና ሰልጠና መመዝግብ አለበት ይላል።

በአፋር ክልል ይህ ህግ ወጥ ድሪግት ተግባራዊ የሚሆነው በአብደፓ የአፋር ብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ መሪነት ስሆን በየቀበሌው አስተዳደሮች አማካኝነት ትዕዛዙ ወደ ህዝብ እንዲወርድ እየተረገ ይገኛል።

በአፋር ክልል ባሉ በ32 ወረዳዎች ይህ ጉዳይ ወቅታዊ እና አሳሳቢ ሆኖ ይገኛል።

Previous Story

ፍርድ ቤቱ በኮሚቴዎቹ ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላለፈ ኮሚቴዎቹ አስገራሚ ታሪካዊ ንግግር አደረጉ (ቢቢኤን ልዪ የችሎት ዘገባ)

Next Story

የህዝበ ሙስሊሙ ኮሚቴ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ የጥብቅና ሙያቸው ኮሚቴዎቹ የጥፋተኝነት ብይን በተላለፈበት ቀን መሰረዙ ታወቀ

Go toTop