በውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በምርጫ እንዲሳተፉ ሊደረግ ነው

June 12, 2013

በዘሪሁን ሙሉጌታ
በተለያዩ የውጪ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው ዜጎች በሀገሪቱ በሚካሄዱ የምርጫ ስርዓት በመሳተፍ ድምፅ እንዲሰጡ ሊደረግ ነው።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ህግና ደንብ መሰረት በአረብ አገራት ፣ በሰሜን አሜሪካ እና በአውሮፓ እንዲሁም ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ በሌሎች አገሮች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ምርጫ መምረጥ የሚችሉበት ዕድል እየተመቻቸ ነው።
በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲያስፖራ ተሳትፎ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ተሊል ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት ምርጫው የሚከናወነው የሀገሪቱን አቅም ባገናዘበ ሁኔታ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚገኙባቸው ማዕከላት ውስጥ የምርጫ ጣቢያዎችን በማደራጀት ዜጎቹ ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን እንዲወጡ ይደረጋል ብለዋል።
አዲስ የተዘጋጀው የዲያስፖራ ፖሊሲ ካካተታቸው ዋና ዋና ጉዳዮች አንዱ በውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በምርጫ እንዲሳተፉ ማድረግ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ቅዳሜ ሰኔ 8 ቀን 2005 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ የዲያስፖራ ፖሊሲ ላይ በውጪ ሀገር ከሚኖሩ፣ ቁጥራቸው ከአንድ ሺ እስከ ሁለት ሺ ከሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ጋር በፖሊሲው ላይ ምክክር እንደሚካሄድ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቁ አይዘነጋም።n

 

ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ የዛሬ ጁን 12 ቀን 2013 ዕትም

Previous Story

ኢትዮጵያ በግብፅ ላይ ተመጣጣኝ የኃይል እርምጃ ለመውሰድ 1ሺ 500 ኪሎ ሜትር የሚወነጨፍ ሚሳኤል መታጠቅ ብቻ ይበቃታል

Next Story

ኮንዶሚኒየም ፎቅ ላይ የወጣውን ጅብ ለማስወጣት በተከፈተ ተኩስ አንድ ወጣት ቆሰለ

Go toTop