በጋሞጎፋ ዞን በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እየታደኑ እየታሰሩ ነው

May 10, 2015

በጋሞጎፋ ዞን በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እየታደኑ እየታሰሩ መሆኑን የዞኑ የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች ገልጸዋል፡፡ ከትናንት ሚያዝያ 30/2007 ዓ.ም ጀምሮ ጋሞ ጎፋ ዞን ጎፋ ወረዳ ሳውላ ከተማው ውስጥ በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች መታሰራቸውን የጋሞ ጎፋ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ በትናንትናው ዕለት በጋሞጎፋ ዞን ዳራማሎ ወረዳ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ 17 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ታስረዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጋሞጎፋ ዞን ቦንኬ ወረዳ ለፖሊስ ‹‹ለሰማያዊ ፓርቲ የሚቀሰቅስ ማንኛውም አካል ላይ እርምጃ ውሰዱ›› የሚል ትዕዛዝ መተላለፉን የዞኑ የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች ገልጸዋል፡፡

Previous Story

በአይሲኤስ የተገደሉትን ቤተሰቦች ያልረዱት ኣላሙዲን ሶስት ዘፋኞችን ሚሊየነር አደረጉ

Next Story

Hiber Radio: ቻይና ለኢትዮጵያው አገዛዝ የጦር መሳሪያ ማስታጠቋን የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ደርሼበታለሁ አለ *የመን ያሉ ኢትዮጵያውያን አገዛዙ ዜጎችን ከመመለስ ይልቅ የውስጥ የቪዛ ንግድ ላይ አተኩሯል ይላሉ * የኢትዮጵያና የደቡብ ሱዳን ባለስልጣናት ተቃዋሚዎቻቸውን ላለማስታጠቅ ለመስማማት ስብሰባ ተቀምጠው እንደነበር ተዘገበ * የኢትዮጵያ መንግስት በእስራኤል መብታቸው የተነካ ኢትዮጵያውያን ቤተ እስራኤሎች ጉዳይ ያሳስበኛል ማለቱን ብዙዎች አጣጣሉት * ኢትዮጵያዊው የታሪክ ተራኪ ኤድዋርዶ ባይሮኖ የሰጠው ቃለምምልስ እና ሌሎችም..

Go toTop