በአፋር ክልል አሳዛኝ የጎርፍ አደጋ ደረሰ

October 12, 2014

አኩ ኢብን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው

በአፈር ክልል በአሚ ባራ ወረዳ በአዋሽ ሸለቆ ከተማና (በባዓዶህ አሞ ቀበሌ፣ በቦናት ቀበሌና በሓሶባ ቀበሌ ትናንት ከሌሊቱ ከ8:00 ሰዓት ጀምሮ ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ደርሷል። ጎርፉ ከጎረቤት ክልል የመጣ ሲሆን በዛ አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎችን ተፈናቅለዋል።
(ፎቶ ፋይል)
በአሁን ሰአት ደግሞ ከሚባራ ወረዳ ዘግይቶ የደረሰን መረጃ እንሚያመለከተው እስካሁን በሰው ህይወት ላይ የደረሰ አደጋ ባይኖርም ነዋሪዎች ከቤታቸው ተፈናቀለው በትምህርት ቤቶች ይገኛሉ። በዛ አካባቢዎች የሚገኙ እርሻዎች ቤቶች እና ቁሳቁሶች ከጥቅም ውጭ ሆነዋል። ከክልልም ሆነ ከፌደራል መንግስት እስካሁን ለእነዚህ አደጋ ለደረሰባቸው ዜጎች የተደረገ እርዳታ የለም።

እስካሁን አማራጭ በማጣት በየትምህርት ቤቶች የገቡት እነዚህ ዜጎች በአደጋ ላይ ይገኛሉ።

Previous Story

”የመናፍቃኑ ተላላኪዎች መሠረተ ቢስ ውንጀላ ከአገልግሎታችን አንዲት ጋት ወደ ኋላ እንደማይመልሰን እንዲታወቅልን እንፈልጋለን” -ማኅበረ ቅዱሳን

Next Story

መኢአድ ታላቅ የተቃዉሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ሊያደርግ ነው

Go toTop