በጎንደር አዘዞ አካባቢ 1250 ኮንደሚኒየም ቤቶችን የተረከቡ አባወራዎች ላለፉት 3 ዓመታት መብራት ማጣታቸውን ገለጹ

October 5, 2014

(ዘ-ሐበሻ) በሰሜን ጎንደር አዘዞ አካባቢ ከ3 ዓመት በፊት የኮንደሚኒየም ቤት የተረከቡ ወገኖች ላለፉት 3 ዓመታት ኮንደሚኒየሞቹ መብራት ያልገባላቸው በመሆኑ በከፍተኛ መጉላላት ላይ እንደሚገኙ ለዘ-ሐበሻ በላኩት አቤቱታ አስታወቁ።

የጎንደር ከተማ (ፎቶ ፋይል)ከ3 ዓመት በፊት 1250 የኮንደሚኒየም ቤቶች ተሰርተው መብራት ሳይገባላቸው ተሰጥቶናል ያሉት ነዋሪዎቹ ገንዘባችንን ከወሰዱ በኋላ መብራት ሳይገባላቸው ይኸው በስቃይ ላይ ነን ብለዋል። “ስጋ ሰጥቶ ቢለዋ እንደመከልከል ነው” የሚሉት ነዋሪዎቹ አካባቢያችን አቋርጦ የሚያልፍ የመብራት ገመዶችን ከማየት ውጭ በመኖሪያ ቤታችን መብራት አትጠናል ይህም “የበይ ተመልካች…” የሚለውን ያስተርታል ይላሉ።

“በአካባቢው የሚገኘውን የመብራት ኃይል ጠይቃችሁ ነበር ወይ ለምን መብራቱ እንደዘገየ?” በሚል ዘ-ሐበሻ ለነዋሪዎቹ ጥያቄ ያቀረበች ሲሆን ነዋሪዎቹ ጥያቄውን በተደጋጋሚ ቢያቀርቡም፤ የሚሰጣቸው ምላሽ ላለፉት 3 ዓመታት ሰበብ ብቻ እንደሆነ ገልጸውልናል።

ዘ-ሐበሻ የአካባቢውን የመብራት ሃይል ባለስልጣን ለምን ባለፉት 3 ዐመታት እነዚህ ኮንደሚኒየም ቤቶች መብራት እንዳላገኙ ለመጠየቅ ሙከራ አድርጋ የነበረ ቢሆን ያገኘችው ምላሽ “ለሚድያ መግለጫ አንሰጥም” የሚል ነው።

Previous Story

የወያኔው ወመኔዎች መንግስት የደህንነት ቡድን በድጋሚ በአዲስ መልክ ተዋቀረ

Next Story

ነገረ ህወሓት: ህወሓትና ‹‹ወያኔ›› ምንና ምን ናቸው? – ጌታቸው ሺፈራው (ጋዜጠኛ)

Go toTop