በደቡብ ኢትዮጵያ ባስኬቶ ወረዳ የመኢአድን ቢሮዎች በካድሬዎች ተሰበሩ

September 16, 2014

ወያኔ በመጭው ምርጫ ባለጠንካራ መዋቅሩ መኢአድ ላይ ያለው ስጋትና ፍርሃት ጨምሯል።

በደቡብ ኢትይጵያ በባስኬት ወረዳ የሚገኘው የመኢአድ ቢሮ በወያኔ ካድሬዎች በሆኑት አቶ ጉልቶ በርቸፌ እና አቶ እርጎ ሃጎስ አስተባባሪነት መሰበራቸውን የድርጅቱ አባላት ለመኢአድ ጽ/ቤት አዲስ አበባ በላኩት ሪፖርት አመልክተዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ቢሮውን ከሰበሩ በኋላ የደኮጨፌ ቀበሌ ሰብሳቢ አቶ ሃይሉ አርጋዉን ክፉኛ በመደብደብ ከፍተኛ ጉዳት አድርስዉባቸዋል፡፡ ሼልካናቦላ ቀበሌን ፓፔላ በመንቀል የመኢአድን የቀበሌዉን ሰብሳቢ አቶ በድሉ ቢጋናን አስረዋቸዋል፡፡ አሁን የተቃዋሚ ድርጅት አባሎችን ማንገላታት ማሰር መግደል አልቆመም ፡፡ወያኔ ኢሕአዲግ ጠንካራ ተቃዋሚ የሚባል በምርጫ ማየት አይፈልግም፡፡

Previous Story

በ 2007 ዓ.ም ለሚደረገው ሃገራዊና ክልላዊ ምርጫ ሚሊሻዎች ልዩ ተልዕኮ እንደተሰጣቸው ተገለጸ

Next Story

Health: የሰውነት መቆጣት (አለርጂ)

Go toTop