ዕውነት ያሸንፋል! የሚለውን መርህ አስቀድማ ወቅታዊ መረጃዎችን ለሕዝብ የማድረስ የ7ኛ ዓመት ጉዞዋን የጀመረችው ዘ-ሐበሻ በየዓመቱ አንባቢዎቿን በማሳተፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በዓመቱ ትልቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን “የዓመቱ ምርጥ ሰው” በማለት ትሰይማለች። ባለፈው 2005 የኢትዮጵያውያን ዘመን የዓመቱ የዘ-ሐበሻ አንባቢያን ምርጥ ሰው ተብሎ የተሰየመው በእስር ላይ የሚገኘው አንዷለም አራጌ ነበር። ዘንድሮም እንዲሁ የ2006 የዓመቱ ምርጥ ሰው ምርጫዎን በየትኛውም ዘርፍ በኢትዮጵያ በዓመቱ ትልቅ ሥራ ሰርቷል የሚሉትን ሰው እንዲመርጡ አንባቢዎቿን ዘ-ሐበሻ ትጠይቃለች።
የዚህን ምርጫ ውጤት ዘ-ሐበሻ ጷጉሜ 2006 ዓ.ም ለአንባቢዎቿ ታቀርባለች።
ምርጫዎን፡ በአስተያየት መስጫ ሳጥን፣ በኢሜይል
info@ethiopoint.com
admin@ethiopoint.com
በስልክ ቁጥር
612 – 986 0557
ላይ መደወል ወይም ቴክስት በመላክ፣ ልታሳውቁን ትችላላችሁ።